መነሻ / የጥቃቅን እና አነስተኛ መረጃ / ወቅታዊ መረጃ / በአዲስ አበባ ከተማ ከመሬትና መሬት ነክ ከሆኑ ጉዳዮች ጋር ተቋርጦ የነበረው የአገልግሎት እገዳ ተነሳ
Addis-Ababa-Land

በአዲስ አበባ ከተማ ከመሬትና መሬት ነክ ከሆኑ ጉዳዮች ጋር ተቋርጦ የነበረው የአገልግሎት እገዳ ተነሳ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከመሬትና መሬት ነክ ከሆኑ ጉዳዮች ጋር ተቋርጦ የነበረው የአገልግሎት እገዳ ከህዳር 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ተነስቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከነሀሴ 20 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ መሬትና መሬት ነክ የሆኑ ጉዳዮች አገልግሎት ላልተወሰነ ጊዜ ማገዱ ይታወሳል።

የከተማ አስተዳደሩ በመሬትና መሬት ነክ ጉዳዮች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ሲያከናውን የነበረውን የማጥራት ሥራዎችን ማጠናቀቅ ተችሏል። በመሆኑም ተጥሎ የነበረው እገዳ ከህዳር 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ የተነሳ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል።

የዜና ምንጭ፡- የአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢሮ የፌስቡክ ገጽ

ይህንንም ይመልከቱ

kefta-care-training-2

ከፍታ ለ20 ኢንተርፕራይዞች ሥልጠና ሰጠ

ከፍታ ከኬር ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለ20 በሴቶች ለሚተዳደሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሥልጠና ሰጠ። ሥልጠናው ያተኮረው …