መነሻ / ፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት / የግል ብድር እና ቁጠባ ተቋማት

የግል ብድር እና ቁጠባ ተቋማት

ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተፕራይዞች ምዝገባ ከፈጸሙ በኋላ እንዲሁም ሥራቸውን እየሠሩ እያለ የፋይናንስ ድጋፍ ቢፈልጉ፣ ድጋፍ የሚያገኙባቸውን የግል ማይክሮፋይናንስ (የአነስተኛ ብድር እና ቁጠባ) ተቋማት አገልግሎቶች ዝርዝርን በዚህ ስር ያገኛሉ።

ልዩ የገንዘብ የእገዛ ተቋም

liyu-logo

ልዩ የገንዘብ የእገዛ ተቋም መንግሥት ባወጣው የአንስተኛ ፋይናንስ አቅራቢ ተቋማት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 40/88 መሠረት በ1989 ዓ.ም. ተመሠረተ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለተቋሙ የሰጠው የፈቃድ ቁጥር MFI/034/2011 ሲሆን የንግድ ምዝገባ ቁጥሩ ደግሞ 06/2/06393/96 ነው። ተቋሙ ከቀደምት ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ውስጥ አንዱ ሲሆን ከ24 ዓመት በላይ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል። በአሁኑ …

ተጨማሪ

የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር

ae-logo

ኅብረት ሥራ ማኅበር ማለት ሰዎች የጋራ ፍላጎታቸውን ለማሳካት ያላቸውን ዕውቀት፣ ጉልበት፣ ጊዜ እና ሀብት በማሰባሰብ ችግሮቻቸውን መፍታት የሚያስችል ቁልፍ መሣሪያ ነው። በዚህ መሠረት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ መሥራች አባላት በሕጋዊ መንገድ የተመሠረተ ማኅበር ነው። መቆጠብ መሰሰት አይደለም!!! ለለውጥ …

ተጨማሪ

ዋን ማይክሮፋይናንስ

ዋን ማይክሮ ፋይናንስ ቀደም ሲል ለታ ማይክሮ ፋይናንስ በመባል ይታወቅ የነበረ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ነው። በብሔራዊ ባንክ ሕግ እና ደንብ መሠረት በአዋጅ ቁጥር 40/1996 (በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 626/2009) የተቋቋመ ሲሆን የማይክሮ ፋይናንስ እና ተያያዥ አገልግሎቶችን ለመስጠት ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ተሰጥቶት ጥቅምት 28 ቀን 1997 (29 October 2004) ዓ.ም. ሥራ ጀምሯል። …

ተጨማሪ

የካቲት 23 የገንዘብ ቁጠባና ብድር

የካቲት 23 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኀላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር ቁጠባን ባሕል አድርጎ በራስ ገንዘብ ሕይወትን መቀየር ይቻላል ብሎ ያምናል። ይህም ይሳካ ዘንድ መደበኛ እና የፈቃድ ቁጠባ ለአባላቱ ያዘጋጀ ሲሆን ለስድስት ወር በተከታታይ በመቆጠብ ብድር መበደር እንዲችሉ ያደርጋል። በዚህም አባላት የራሳቸውን፣ የቤተሰባቸውን ብሎም የአገራቸውን የእድገት ለውጥ እንዲያፋጥኑ የሚያደርግ ተቋም ነው።

ተጨማሪ

ቤተ-ሐበሻ ቁጠባ እና ብድር ኀላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር

ኅብረት ሥራ ማኅበር ሰዎች የጋራ ፍላጎታቸውን ለማሳካት ያላቸውን ዕውቀት፣ ጉልበት፣ ጊዜ እና ሀብት በማሰባሰብ ችግሮቻቸውን መፍታት የሚያስችል ቁልፍ መሣሪያ ነው። በዚህ መሠረት ቤተ-ሐበሻ ቁጠባ እና ብድር ኀላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ መሥራች አባላት በሕጋዊ መንገድ የተመሠረተ የኅብረት ሥራ ማኅበር ነው።

ተጨማሪ

ጊዜ የገንዘብ ቁጠባና ብድር

ጊዜ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር በሕግ ታውቆ በምዝገባ ቁጥር ቦሌ/1/1234/2013 የተመዘገበ ለመሆኑ የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ ወረቀት በኅዳር 15 ቀን፣ 2013 ዓ.ም. ተሰጥቶት ሥራ ጀምሯል።

ተጨማሪ

አማራጭ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር

አማራጭ የኮድ 3 ሜትር ታክሲ እና የኮድ አንድ ታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር ኅብረተ ሰቡ ከሚያገኘው ገቢ ላይ የተወሰነ ገንዘብ በመቆጠብ ራሱን በራሱ እንዲረዳና የቁጠባን ባሕል በማዳበር ፈጣን የሆነ የብድር አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል ታኅሳስ 9 ቀን፣ 2014 ዓ.ም. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 50 አባላትን …

ተጨማሪ

ቤተል የገንዘብ ቁጠባና ብድር

credit-and-saving

ቤተል የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኀበር የተቋቋመው በኢትዮጵያ የኀብረት ሥራ ማኅበር አዋጅ መሠረት በቁጥር 985/2009 ሲሆን፤ ሕጋዊ ሰውነት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኀብረት ሥራ ኤጀንሲ በነሐሴ 2005 ዓ.ም. ፈቃድ አግኝቶ በሥራ ላይ ይገኛል። “ቤተል ውስጥ ሁላችንም አለን!!”

ተጨማሪ

ቀንዲል ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ.

kendi-logo

ቀንዲል በአብዛኛው ሀገሪቱ ክልሎች በከተማና በገጠር የሚኖሩ ለሥራ ተነሳሽነት ያላቸው ዜጎች በተለይም ለባንክ አገልግሎት ዕድል ለተነፈጉ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ነጋዴዎችና አርሶ አደሮች የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ከብሔራዊ ባንክ ፍቃድ በማግኘት የተቋቋመ ነው። ለቁም ነገር ተበደሩ፣ በጊዜው ክፈሉ፣ ዘወትር ቆጥቡ!

ተጨማሪ