መነሻ / የቢዝነስ ዜና

የቢዝነስ ዜና

በዚህ ስር የቢዝነስ ዜናዎች ይቀርባሉ።

ከፍታ ለ20 ኢንተርፕራይዞች ሥልጠና ሰጠ

kefta-care-training-2

ከፍታ ከኬር ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለ20 በሴቶች ለሚተዳደሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሥልጠና ሰጠ። ሥልጠናው ያተኮረው ኢንተርፕራይዞቹ በኬር ኢትዮጵያ በተመቻቸላቸው ዕድል የ”ከፍታ” አገልግሎትን ተጠቅመው እንዴት የጨረታ መረጃዎችን በቀላሉ ማግኘት እንደሚችሉ በተጨማሪም እንዴት አድርገው ድርጅታቸውን፣ ምርታቸውን እና አግልግሎታቸውን እንደሚያስተዋውቁ ነው።

ተጨማሪ

ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት 5.5 ቢሊዮን ብር ከአዋሽ ባንክ በብድር ሊያገኙ ነው

አዋሽ ባንክ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ውስጥ ለተለያዩ የማክሮ ፋይናንስ ተቋማት 5.5 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ። ባንኩ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ለማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት (ለአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት) ለማበደር ካቀደው በጀት ውስጥ 1.5 ቢሊዮን ብር የሚሆነውን ብድር ተጠቃሚ ከሚሆኑ ዘጠኝ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ጋር ባለፈው ሐሙስ ሐምሌ 21 ቀን …

ተጨማሪ

የሮያሊቲ ክፍያ ለባህላዊ ወርቅ አምራቾች ሙሉ በሙሉ ተነሳላቸው

artisanal-miner

በባህላዊ መንገድ ወርቅ እያመረቱ ለባንክ የሚያቀርቡ አምራቾች ለክልል ሲከፍሉ የነበረው የሮያሊቲ ክፍያ ሙሉ በሙሉ በክልሎች ርዕሰ መስተዳድሮች መነሳቱ ተገለጸ። ይህን የገለጹት የማዕድን እና የኢነርጂ ሚኒስትሩ ታከለ ኡማ (ኢ/ር) በፌስቡክ ገጻቸው ነው፤ ውሳኔውንም የሚመሰገን ነው ያሉት ሚኒስትሩ አክለውም “ይህ እርምጃ ለባህላዊ የማዕድን ምርት እንደሀገር የሰጠነው ትኩረት ማሳያ ነው” ብለዋል። የባህላዊ እና …

ተጨማሪ

የከተማ ግብርና፦ በአዲስ አበባ በዘንድሮው የመኸር ወቅት ከ5000 ሄክታር በላይ መሬት ሙሉ በሙሉ በዘር ተሸፈነ

የከተማ-ግብርና

በአዲስ አበባ ከተማ በዘንድሮው የመኸር ወቅት ከአምስት ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ሙሉ በሙሉ በዘር መሸፈኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአርሶ አደሮችና ከተማ ግብርና ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር መኮንን ሌንጅሶ ከቦሌ ክፍለ ከተማ አመራሮች ጋር በመሆን የከተማ ግብርና የሥራ እንቅስቃሴን በቦሌ ክፍለ ከተማ በመገኘት የመስክ ጉብኝት አድርገዋል።

ተጨማሪ

የኢንተርፕራይዞችን የገበያ ትስስር ለማሳደግ ኤግዚብሽንና ባዛር ጠቃሚ መሆኑ ተገለጸ

BoJCED-Tamiru-Debela

በኮቪድ ተፅዕኖ ተቀዛቅዞ የነበረውን የኢንተርፕራይዞችን የገበያ ትስስር ለማሳደግ ኤግዚብሽንና ባዛር ጠቃሚ መሆኑን የአዲስ አበባ የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ገለጸ። በ2014 አዲስ ዓመት ዋዜማ ኤግዚብሽንና ባዛር በዐሥራ አንዱም ክፍለ ከተሞች አንድ ሺህ ዐሥር ኢንተርፕራይዞች መሳተፋቸውን በቢሮው የገበያ ልማትና ግብይት ዳይሬክቶሬት ገልጿል፡፡

ተጨማሪ

በኮቪድ-19 ለተጎዱ ኢንተርፕራይዞች የሚውል 207 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ስምምነት ተፈረመ

ዛሬ በገንዘብ ሚኒሰቴር በተደረገ የፊርማ ስነ-ሰርዓት ላይ በኢትዮጰያ መንግስት እና በዓለም ባንክ የ907 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈረመ። ከዚህ ውስጥ 200 ሚሊዮን ዶላር በኢትዮጵያ ውስጥ በአነስተኛ እና ጥቃቅን ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሚውል ነው። የ200 ሚሊዮን ዶላሩ ድጋፍ ዒላማ ያደረገው በተለይ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ክፉኛ ተጎድተው፣ ነገር ግን ቢደገፉ በሥራቸው አዋጭ ሆነው …

ተጨማሪ

ከፍታ ማዕከል በስዊድን እና ኔዘርላንድስ ኤምባሲዎች እና የአውሮፓ ኅብረት ልዑካን ቡድን ተጎበኘ

kefta-april-delegates-visit

ሐሙስ መጋቢት 30፣ 2013 ዓ.ም የከፍታ ማዕከል ከስዊድን እና ከኔዘርላንድስ ኤምባሲዎች፣ እንዲሁም ከአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ ልዑክ የመጡ ጎብኚዎችን አስተናግዷል። ጉብኝቱ የተካሄደው የከፍታ አጋር በሆነው የኔዘርላንድስ በጎ አድራጎት ድርጅት ኤስኤንቪ (SNV) እና ከሴቶች እና ወጣቶች ጋር በተያያዘ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሊዌይ (LI-WAY) አስተባባሪነት ነው። በጉብኝቱ ወቅት ለተገኙት በኢትዮጵያ የስዊድን አምባሳደር ሃንስ …

ተጨማሪ

የማምረቻ ተቋማት የሚያጋጥማቸውን የኃይል አቅርቦት ችግር ሊፈታ የሚያስችል የስምምነት ሰነድ ተፈረመ

electric-power

በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መካከል የማምረቻ ተቋማት የሚያጋጥማቸውን የኃይል አቅርቦት ችግር ሊፈታ የሚያስችል የስምምነት ሰነድ ተፈረመ። የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት የማምረቻ ኢንዱስትሪ ተቋማት የሚያጋጥማቸውን የኃይል አቅርቦት ችግር ሊፈታ የሚያስችልና ሁለቱ ተቋማት ሀገራዊና ተቋማዊ ሥራዎችን በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ነው።

ተጨማሪ

መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ምርቱን ለገበያ ማቅረብ ጀመረ

በህግ ማስከበር ዘመቻው ምክንያት ባለፉት አራት ወራት ሥራ አቁሞ የነበረው በትግራይ ክልል የሚገኘው መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ የማምረት ሥራውን በመጀመር ምርቱን ለገበያ እያቀረበ መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ። ፋብሪካው ምርቱን ለገበያ ማቅረብ መጀመሩ ወደላይ ወጥቶ የነበረውን ዋጋ  ለማሻሻል የራሱ የሆነ አዎንታዊ ሚና  እንደሚኖረው ጨምረው ተናግረዋል።

ተጨማሪ