ታዳጊ መካከለኛ

ወደ ታዳጊ መካከለኛ ደረጃ ለማደግ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች

በኢንዱስትሪ ዘርፍ ለተሰማራ ጥቃቅን/አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ

  1. በሥራ ዕድል ፈጠራ
    • የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ ከ30 ሰዎች በላይ
    • የፈጠረው ጊዜያዊ የሥራ ዕድል በዓመት ውስጥ ከ20 ሰዎች በላይ
  2. በሃብት መጠን
    • ጠቅላላ ሃብት ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ (የተጣራ ሃብት እና እዳን ጨምሮ)
    • በብድር ካገኘው ገንዘብ ቢያንስ 70% ለቋሚ ንብረት ያዋለ
    • የሃብት እና የእዳ መግለጫ (ኦዲት ሪፖርት) ህጋዊ እውቅና ባለው ኦዲተር ያረጋገጠ
  3. በትርፋማነት
    • በ1 ዓመት ካደረገው ሽያጭ እስከ 30% ትርፍ ያስመዘገበ
    • ከትርፉ ላይ ለሥራ ማስፋፊያ ያዋለው ወይም የቆጠበው፣ ከተጣራ ሃብቱ ቢያንስ 50% የሆነ
  4. በገበያ መጠን
    • የ1 ዓመት ሽያጩ ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ
    • እንደየ ንዑስ ዘርፉ፣ ተከታዩ መጠን ሽያጭ ከመንግስት የገበያ ትስስር ውጪ የሆነ
      • ኮንስትራክሽን – ቢያንስ 50%
      • ብረታ ብረትና እንጨት – ቢያንስ 80%
      • ሌሎች ንዑስ ዘርፎች – ቢያንስ 90%
    • ለሌሎች ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በንዑስ ኮንትራት በ1 ዓመት ቢያንስ 5 ጊዜ የገበያ ትስስር የፈጠረ
    • ቢያንስ አምስት ዓይነት ውጤታማ የማስተዋወቂያ ዘዴዎችን የተጠቀመ
    • ለደረጃው በተዘጋጀ ኤግዚቢሽንና ባዛር ቢያንስ በዓመት ሁለቴ የተሳተፈ
  5. በምርታማነት
    • ካለው ሙሉ የማምረት አገልግሎት የመስጠት አቅም ቢያንስ 85% የተጠቀመ
    • ለሚያመርታቸው ምርቶችና አገልግሎቶች ዘመናዊ የሥራ አመራርን የተከተለ የቁጥጥር ሥርዓት የዘረጋ
    • ለገቢ ወይም ለወጪ ምርቶች የሚውሉ ግብዓቶችን ወይም ገቢ ምርቶችን የሚተካ፣ ወይም ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን ማምረት የቻለ
    • ከኢንተርፕራይዙ አባላት ወይም ቋሚ ሠራተኞች ውስጥ ቢያንስ 90% ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት ያላቸው
  6. በተቋማዊ አመራርና አደረጃጀት
    • ዘመናዊ የሥራ አመራር ዘይቤ ተግባራዊ ያደረገና ስትራቴጂክ ዕቅድ ያለው
    • የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ሥራ ላይ ያዋለና ኦዲት ያስደረገ
    • የማምረቻ ማዕከሉ አደረጃጀት የምርት ሂደትን የተከተለና ንጽሕናውን የጠበቀ
    • የሠራተኞችን የሥራ ደህንነት ለመጠበቅ የሥራ ልብስ እና እንደ ንዑስ ዘርፉ ዓይነት የደህንነት መሣሪያዎች የተሟሉለት
    • ሥራውን ሊያስፋፋ የሚያስችል በጽሑፍ የተዘጋጀ የንግድ ዕቅድ ያለው
    • ከሌሎች ኢንተርፕራይዞች ጋር ሃሳብ ለመለዋወጥም ሆነ በጋራ ለመንቀሳቀስ የሚያስችል የንግድ ግንኙነት የፈጠረ
  7. በመንግስታዊ ድጋፎች አጠቃቀም
    • የሚሰጠውን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ተግባር ላይ አውሎ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣና የአሠራሩን ተሞክሮ ለሌሎች ማካፈል የሚችል
    • ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም ጋር በትብብርና በኩባንያ ውስጥ ስልጠና የሚሳተፍ
    • ተደጋጋሚ የብድር ተጠቃሚ ሆኖ ያልተመለሰ ውዝፍ ብድር የሌለበት
    • የማምረቻ ማዕከል ተጠቃሚ ከሆነ፣ የውል ግዴታውን በአግባቡ የተወጣ
    • በመንግስት የሚሰጠውን የገበያ ትስስር በገባው ውል መሠረት በአግባቡ እየሠራ ያለ ወይም ሠርቶ ያስረከበ
    • ወደ ኢንዱስትሪ ዞን ለመግባት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ያጠናቀቀ
    • ከንግድና ልማት ባንኮች ለመበደር የሚያስችል የብድር ዋስትና ያዘጋጀ
  8. በቴክኖሎጂ አጠቃቀም
    • ምርቱን ወይም አገልግሎቱን ለማሻሻል በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት፣ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ተቋማት የሚሰራጩ ተፈላጊና አዋጪ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ የሆነ
    • የምርትና አገልግሎት ጥራትን ለመቆጣጠር የሚያስችል ወቅታዊና የተሻሻለ አሠራር ተጠቃሚ የሆነ
    • ከሚጠቀምባቸው የማምረቻ ወይም የአግልግሎት መስጫ መሣሪያዎች ውስጥ ቢያንስ 85% የአካባቢ ብክለት የማያስከትሉና ኃይል ቆጣቢ የሆኑ
  9. ግዴታን ስለመወጣት
    • የሚጠበቅበትን የ1 ዓመት ገቢ ግብር የከፈለ
    • ዓመታዊ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ እድሳት ያካሄደ
    • የተሠጠውን የዕድገት ደረጃ ሰርቲፊኬት የመለሰ

በአገልግሎት ዘርፍ ለተሰማራ ጥቃቅን/አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ

  1. በሥራ ዕድል ፈጠራ
    • የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ ከ20 ሰዎች በላይ
    • የፈጠረው ጊዜያዊ የሥራ ዕድል በዓመት ውስጥ ከ15 ሰዎች በላይ
  2. በሃብት መጠን
    • ጠቅላላ ሃብት ከ500,000 ብር በላይ (የተጣራ ሃብት እና እዳን ጨምሮ)
    • በብድር ካገኘው ገንዘብ ቢያንስ 40% ለቋሚ ንብረት ያዋለ
    • የሃብት እና የእዳ መግለጫ (ኦዲት ሪፖርት) ህጋዊ እውቅና ባለው ኦዲተር ያረጋገጠ
  3. በትርፋማነት
    • በ1 ዓመት ካደረገው ሽያጭ ቢያንስ 30% ትርፍ ያስመዘገበ
    • ከትርፉ ላይ ቢያንስ ለሥራ ማስፋፊያ ያዋለው ወይም የቆጠበው፣ ከተጣራ ሃብቱ ቢያንስ 30% የሆነ
  4. በገበያ መጠን
    • የ1 ዓመት ሽያጩ ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ
    • ከሽያጩ ቢያንስ 90% ከመንግስት የገበያ ትስስር ውጪ የተገኘ
    • ቢያንስ አምስት ዓይነት ውጤታማ የማስተዋወቂያ ዘዴዎችን የተጠቀመ
  5. በምርታማነት
    • ካለው ሙሉ የማምረት አገልግሎት የመስጠት አቅም ቢያንስ 85% የተጠቀመ
    • ለሚያመርታቸው ምርቶችና አገልግሎቶች ዘመናዊ የሥራ አመራርን የተከተለ የቁጥጥር ሥርዓት የዘረጋ
    • ለገቢ ወይም ለወጪ ምርቶች የሚውሉ ግብዓቶችን ወይም ገቢ ምርቶችን የሚተካ፣ ወይም ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን ማምረት የቻለ
    • ከኢንተርፕራይዙ አባላት ወይም ቋሚ ሠራተኞች ውስጥ ቢያንስ 90% ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት ያላቸው
  6. በተቋማዊ አመራርና አደረጃጀት
    • ዘመናዊ የሥራ አመራር ዘይቤ ተግባራዊ ያደረገና ስትራቴጂክ ዕቅድ ያለው
    • የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ሥራ ላይ ያዋለና ኦዲት ያስደረገ
    • የማምረቻ ማዕከሉ አደረጃጀት የምርት ሂደትን የተከተለና ንጽሕናውን የጠበቀ
    • የሠራተኞችን የሥራ ደህንነት ለመጠበቅ የሥራ ልብስ እና እንደ ንዑስ ዘርፉ ዓይነት የደህንነት መሣሪያዎች የተሟሉለት
    • ሥራውን ሊያስፋፋ የሚያስችል በጽሑፍ የተዘጋጀ የንግድ ዕቅድ ያለው
    • ከሌሎች ኢንተርፕራይዞች ጋር ሃሳብ ለመለዋወጥም ሆነ በጋራ ለመንቀሳቀስ የሚያስችል የንግድ ግንኙነት የፈጠረ
  7. በመንግስታዊ ድጋፎች አጠቃቀም
    • የሚሰጠውን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ተግባር ላይ አውሎ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣና የአሠራሩን ተሞክሮ ለሌሎች ማካፈል የሚችል
    • ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም ጋር በትብብርና በኩባንያ ውስጥ ስልጠና የሚሳተፍ
    • ተደጋጋሚ የብድር ተጠቃሚ ሆኖ ያልተመለሰ ውዝፍ ብድር የሌለበት
    • የማምረቻ ማዕከል ተጠቃሚ ከሆነ፣ የውል ግዴታውን በአግባቡ የተወጣ
    • በመንግስት የሚሰጠውን የገበያ ትስስር በገባው ውል መሠረት በአግባቡ እየሠራ ያለ ወይም ሠርቶ ያስረከበ
    • ወደ ኢንዱስትሪ ዞን ለመግባት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ያጠናቀቀ
    • ከንግድና ልማት ባንኮች ለመበደር የሚያስችል የብድር ዋስትና ያዘጋጀ
  8. በቴክኖሎጂ አጠቃቀም
    • ምርቱን ወይም አገልግሎቱን ለማሻሻል በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት፣ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ተቋማት የሚሰራጩ ተፈላጊና አዋጪ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ የሆነ
    • የምርትና አገልግሎት ጥራትን ለመቆጣጠር የሚያስችል ወቅታዊና የተሻሻለ አሠራር ተጠቃሚ የሆነ
    • ከሚጠቀምባቸው የማምረቻ ወይም የአግልግሎት መስጫ መሣሪያዎች ውስጥ ቢያንስ 85% የአካባቢ ብክለት የማያስከትሉና ኃይል ቆጣቢ የሆኑ
  9. ግዴታን ስለመወጣት
    • የሚጠበቅበትን የ1 ዓመት ገቢ ግብር የከፈለ
    • ዓመታዊ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ እድሳት ያካሄደ
    • የተሠጠውን የዕድገት ደረጃ ሰርቲፊኬት የመለሰ

ወደ ታዳጊ መካከለኛ ኢንዱስትሪ የመሸጋገር ሂደት

እንዲህ ዓየነቱ ሽግግር ዘርፍካፒታል እና ኢንተርፕራይዙ የፈጠረውን የሥራ ዕድል መሠረት ያደረገ ነው።

በኢንዱስትሪ ዘርፍ ለተሰማራ ኢንተርፕራይዝ

  • ካፒታሉ ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ (በማስረጃ የተረጋገጠ)
  • የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ ከ30 ሰው በላይ
  • የፈጠረው ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከ20 ሰው በላይ

በአገልግሎት ዘርፍ ለተሰማራ ኢንተርፕራይዝ

  • ካፒታሉ ከ500 ሺህ ብር በላይ (በማስረጃ የተረጋገጠ)
  • የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ ከ20 ሰው በላይ
  • የፈጠረው ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከ15 ሰው በላይ

ማስታወሻ፦ ይሄ መረጃ የተዘጋጀው ቀድሞ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ አሁን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽሕፈት ቤት በተገኘው መረጃ ላይ ተመሥርቶ ለጥቃቅን እና አነስተኛ ድርጅቶች በሚጠቅም መልኩ ተቀናብሮ ነው።

ይህንንም ይመልከቱ

industry

ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ዕድገት ደረጃ

ወደ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ዕድገት ደረጃ የሚሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች በሥራ ዕድል ፈጠራ ሀ) በኢንዲስትሪ …