kefta

መብቃት

ወደ መብቃት ደረጃ ለማደግ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች

በኢንዱስትሪ ዘርፍ ለተሰማራ ጥቃቅን/አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ

  1. በሥራ ዕድል ፈጠራ
    • የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል፡-
      • ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ እስከ 5 ሰዎች የቀጠረ
      • ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ ከ 6 እስከ 15 ሰዎች የቀጠረ
    • የፈጠረው ጊዜያዊ የሥራ ዕድል፡-
      • ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ በዓመት ውስጥ እስከ 3 ሰዎች የቀጠረ
      • ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ በዓመት ውስጥ ከ3 እስከ 15 ሰዎች የቀጠረ
  2. በሃብት መጠን
    • ጠቅላላ ሃብት ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ከ75,001 እስከ 100,000 ብር (የተጣራ ሃብት እና እዳን ጨምሮ)
    • ጠቅላላ ሃብት ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ከ500,001 እስከ 1,500,000 ብር (የተጣራ ሃብት እና እዳን ጨምሮ)
    • በብድርም ሆነ በራሱ ገንዘብ ሥራ ለጀመረ፣ ካገኘው ሃብት ቢያንስ 50% ለቋሚ ንብረት ያዋለ
    • ቋሚ ንብረት ኖሮት ለግብዓት የሚበደር፣ ብድሩን ሙሉ በሙሉ ለሥራ ያዋለ
    • በብድርም ሆነ በራሱ ገንዘብ ሥራ ለጀመረ፣ ካገኘው ሃብት ቢያንስ 50% ለቋሚ ንብረት ያዋለ
    • ቋሚ ንብረት ኖሮት ለግብዓት የሚበደር፣ ብድሩን ሙሉ በሙሉ ለሥራ ያዋለ
    • የሃብት እና የእዳ መግለጫ (ኦዲት ሪፖርት) ህጋዊ እውቅና ባለው ኦዲተር ያረጋገጠ
  3. በትርፋማነት
    • በ1 ዓመት ካደረገው ሽያጭ ቢያንስ 20% ትርፍ ያስመዘገበ
    • ከትርፉ ላይ ለሥራ ማስፋፊያ ያዋለው ወይም የቆጠበው፣ ከተጣራ ሃብቱ ቢያንስ 30% የሆነ
  4. በገበያ መጠን
    • የ1 ዓመት ሽያጩ፡-
      • ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ከ75,000 እስከ 100,000 ብር የሆነ
      • ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ከ500,001 እስከ 1,500,000 ብር የሆነ
    • እንደየ ንዑስ ዘርፉ፣ ተከታዩ መጠን ሽያጭ ከመንግስት የገበያ ትስስር ውጪ የሆነ
      • ኮንስትራክሽን – ቢያንስ 35%
      • ብረታ ብረትና እንጨት – ቢያንስ 75%
      • ሌሎች ንዑስ ዘርፎች – ቢያንስ 80%
    • ለሌሎች ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በንዑስ ኮንትራት በ1 ዓመት ቢያንስ 2 ጊዜ የገበያ ትስስር የፈጠረ
    • ቢያንስ አምስት ዓይነት ውጤታማ የማስተዋወቂያ ዘዴዎችን የተጠቀመ
    • ለደረጃው በተዘጋጀ ኤግዚቢሽንና ባዛር ቢያንስ በዓመት ሦስቴ የተሳተፈ
  5. በምርታማነት
    • ካለው ሙሉ የማምረት አገልግሎት የመስጠት አቅም ቢያንስ 70% የተጠቀመ
    • ለሚያመርታቸው ምርቶችና አገልግሎቶች ዘመናዊ የሥራ አመራርን የተከተለ የቁጥጥር ሥርዓት የዘረጋ
    • ለገቢ ወይም ለወጪ ምርቶች የሚውሉ ግብዓቶችን ወይም ገቢ ምርቶችን የሚተካ፣ ወይም ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን ማምረት የቻለ
    • ከኢንተርፕራይዙ አባላት ወይም ቋሚ ሠራተኞች ውስጥ ቢያንስ 75% ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት ያላቸው
  6. በተቋማዊ አመራርና አደረጃጀት
    • ዘመናዊ የሥራ አመራር ዘይቤ ተግባራዊ ያደረገና ስትራቴጂክ ዕቅድ ያለው
    • የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ሥራ ላይ ያዋለና ኦዲት ያስደረገ
    • የማምረቻ ማዕከሉ አደረጃጀት የምርት ሂደትን የተከተለና ንጽሕናውን የጠበቀ
    • የሠራተኞችን የሥራ ደህንነት ለመጠበቅ የሥራ ልብስ እና እንደ ንዑስ ዘርፉ ዓይነት የደህንነት መሣሪያዎች የተሟሉለት
    • ሥራውን ሊያስፋፋ የሚያስችል በጽሑፍ የተዘጋጀ የንግድ ዕቅድ ያለው
    • ከሌሎች ኢንተርፕራይዞች ጋር ሃሳብ ለመለዋወጥም ሆነ በጋራ ለመንቀሳቀስ የሚያስችል የንግድ ግንኙነት የፈጠረ
  7. በመንግስታዊ ድጋፎች አጠቃቀም
    • የሚሰጠውን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ተግባር ላይ አውሎ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣና የአሠራሩን ተሞክሮ ለሌሎች ማካፈል የሚችል
    • ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም ጋር በትብብርና በኩባንያ ውስጥ ስልጠና የሚሳተፍ
    • ተደጋጋሚ የብድር ተጠቃሚ ሆኖ ያልተመለሰ ውዝፍ ብድር የሌለበት
    • የመሥሪያ ቦታ ተጠቃሚ ከሆነ፡-
      • የውል ግዴታውን በአግባቡ የተወጣ
      • የኪራይ ውዝፍ ዕዳ የሌለበት
      • ከማዕከሉ ከመውጣቱ በፊት አስፈላጊውን የፋይናንስና የማምረቻ ቦታ ቅድመ ዝግጅት ያደረገ
      • በመንግስት የሚሰጠውን የገበያ ትስስር በገባው ውል መሠረት በአግባቡ እየሠራ ያለ ወይም ሠርቶ ያስረከበ
  8. በቴክኖሎጂ አጠቃቀም
    • ምርቱን ወይም አገልግሎቱን ለማሻሻል በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት፣ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ተቋማት የሚሰራጩ ተፈላጊና አዋጪ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ የሆነ
    • የምርትና አገልግሎት ጥራትን ለመቆጣጠር የሚያስችል ወቅታዊና የተሻሻለ አሠራር ተጠቃሚ የሆነ
    • ከሚጠቀምባቸው የማምረቻ ወይም የአግልግሎት መስጫ መሣሪያዎች ውስጥ ቢያንስ 75% የአካባቢ ብክለት የማያስከትሉና ኃይል ቆጣቢ የሆኑ
  9. ግዴታን ስለመወጣት
    • የሚጠበቅበትን የ1 ዓመት ገቢ ግብር የከፈለ
    • ዓመታዊ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ እድሳት ያካሄደ
    • የተሠጠውን የዕድገት ደረጃ ሰርቲፊኬት የመለሰ

በአገልግሎት ዘርፍ ለተሰማራ ጥቃቅን/አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ

  1. በሥራ ዕድል ፈጠራ
    • የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል፡-
      • ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ እስከ 5 ሰዎች የቀጠረ
      • ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ ከ 6 እስከ 15 ሰዎች የቀጠረ
    • የፈጠረው ጊዜያዊ የሥራ ዕድል፡-
      • ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ እስከ 2 ሰዎች የቀጠረ
      • ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ከ 2 እስከ 15 ሰዎች የቀጠረ
  2. በሃብት መጠን
    • ጠቅላላ ሃብት ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ከ40,001 እስከ 50,000 ብር (የተጣራ ሃብት እና እዳን ጨምሮ)
    • ጠቅላላ ሃብት ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ከ50,001 እስከ 500,000 ብር (የተጣራ ሃብት እና እዳን ጨምሮ)
    • በብድርም ሆነ በራሱ ገንዘብ ሥራ ለጀመረ፣ ካገኘው ሃብት ቢያንስ 20% ለቋሚ ንብረት ያዋለ
    • ቋሚ ንብረት ኖሮት ለግብዓት የሚበደር፣ ብድሩን ሙሉ በሙሉ ለሥራ ያዋለ
  3. በትርፋማነት
    • በ1 ዓመት ካደረገው ሽያጭ ቢያንስ 20% ትርፍ ያስመዘገበ
    • ከትርፉ ላይ ለሥራ ማስፋፊያ ያዋለው ወይም የቆጠበው፣ ከተጣራ ሃብቱ ቢያንስ 20% የሆነ
  4. በገበያ መጠን
    • የ1 ዓመት ሽያጩ፡-
      • ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ከ50,001 እስከ 75,000 ብር የሆነ
      • ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ከ200,001 እስከ 750,000 ብር የሆነ
    • ከሽያጩ ቢያንስ 85% ከመንግስት የገበያ ትስስር ውጪ የተገኘ
    • ቢያንስ አምስት ዓይነት ውጤታማ የማስተዋወቂያ ዘዴዎችን የተጠቀመ
  5. በምርታማነት
    • ካለው ሙሉ የማምረት አገልግሎት የመስጠት አቅም ቢያንስ 70% የተጠቀመ
    • ለሚያመርታቸው ምርቶችና አገልግሎቶች ዘመናዊ የሥራ አመራርን የተከተለ የቁጥጥር ሥርዓት የዘረጋ
    • ለገቢ ወይም ለወጪ ምርቶች የሚውሉ ግብዓቶችን ወይም ገቢ ምርቶችን የሚተካ፣ ወይም ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን ማምረት የቻለ
    • ከኢንተርፕራይዙ አባላት ወይም ቋሚ ሠራተኞች ውስጥ ቢያንስ 75% ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት ያላቸው
  6. በተቋማዊ አመራርና አደረጃጀት
    • ዘመናዊ የሥራ አመራር ዘይቤ ተግባራዊ ያደረገና ስትራቴጂክ ዕቅድ ያለው
    • የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ሥራ ላይ ያዋለና ኦዲት ያስደረገ
    • የማምረቻ ማዕከሉ አደረጃጀት የምርት ሂደትን የተከተለና ንጽሕናውን የጠበቀ
    • የሠራተኞችን የሥራ ደህንነት ለመጠበቅ የሥራ ልብስ እና እንደ ንዑስ ዘርፉ ዓይነት የደህንነት መሣሪያዎች የተሟሉለት
    • ሥራውን ሊያስፋፋ የሚያስችል በጽሑፍ የተዘጋጀ የንግድ ዕቅድ ያለው
    • ከሌሎች ኢንተርፕራይዞች ጋር ሃሳብ ለመለዋወጥም ሆነ በጋራ ለመንቀሳቀስ የሚያስችል የንግድ ግንኙነት የፈጠረ
  7. በመንግስታዊ ድጋፎች አጠቃቀም
    • የሚሰጠውን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ተግባር ላይ አውሎ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣና የአሠራሩን ተሞክሮ ለሌሎች ማካፈል የሚችል
    • ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም ጋር በትብብርና በኩባንያ ውስጥ ስልጠና የሚሳተፍ
    • ተደጋጋሚ የብድር ተጠቃሚ ሆኖ ያልተመለሰ ውዝፍ ብድር የሌለበት
    • የመሥሪያ ቦታ ተጠቃሚ ከሆነ፡-
      • የውል ግዴታውን በአግባቡ የተወጣ
      • የኪራይ ውዝፍ ዕዳ የሌለበት
      • ከማዕከሉ ከመውጣቱ በፊት አስፈላጊውን የፋይናንስና የማምረቻ ቦታ ቅድመ ዝግጅት ያደረገ
      • በመንግስት የሚሰጠውን የገበያ ትስስር በገባው ውል መሠረት በአግባቡ እየሠራ ያለ ወይም ሠርቶ ያስረከበ
  8. በቴክኖሎጂ አጠቃቀም
    • ምርቱን ወይም አገልግሎቱን ለማሻሻል በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት፣ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ተቋማት የሚሰራጩ ተፈላጊና አዋጪ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ የሆነ
    • የምርትና አገልግሎት ጥራትን ለመቆጣጠር የሚያስችል ወቅታዊና የተሻሻለ አሠራር ተጠቃሚ የሆነ
    • ከሚጠቀምባቸው የማምረቻ ወይም የአግልግሎት መስጫ መሣሪያዎች ውስጥ ቢያንስ 75% የአካባቢ ብክለት የማያስከትሉና ኃይል ቆጣቢ የሆኑ
  9. ግዴታን ስለመወጣት
    • የሚጠበቅበትን የ1 ዓመት ገቢ ግብር የከፈለ
    • ዓመታዊ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ እድሳት ያካሄደ
    • የተሠጠውን የዕድገት ደረጃ ሰርቲፊኬት የመለሰ

ማስታወሻ፦ ይሄ መረጃ የተዘጋጀው ቀድሞ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ አሁን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽሕፈት ቤት በተገኘው መረጃ ላይ ተመሥርቶ ለጥቃቅን እና አነስተኛ ድርጅቶች በሚጠቅም መልኩ ተቀናብሮ ነው።

ይህንንም ይመልከቱ

industry

ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ዕድገት ደረጃ

ወደ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ዕድገት ደረጃ የሚሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች በሥራ ዕድል ፈጠራ ሀ) በኢንዲስትሪ …