መነሻ / ፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት / የግል ብድር እና ቁጠባ ተቋማት / አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የህብረት ሥራ ማኅበር

አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የህብረት ሥራ ማኅበር

አዋጭ ለአነስተኛ የንግድ ሥራ እስከ ብር 400,000 (አራት መቶ ሺህ) ድረስ የሚያበድር ሲሆን ለንግድ መኪና ደግሞ እስከ ብር 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ድረስ ያበድራል።

ለመበደር ምን ማድረግ አለብኝ?

ለአነስተኛ ንግድ ሥራ ብድር አባል ሆኖ ቢያንስ ለ6 (ስድስት) ወራት በተከታታይ መቆጠብ ይኖርበታል። የሚበደረውን ገንዘብ መጠን 25% (አንድ አራተኛ) መቆጠብ አለበት።

የንግድ መኪና ለመግዛት ለሚሰጥ ብድር አባል ሆኖ ቢያንስ ለ 12 (ዐሥራ ሁለት) ወራት በተከታታይ መቆጠብ ይኖርበታል ። የሚበደረውን ገንዘብ መጠን 40% (አርባ በመቶ) መቆጠብ አለበት።

አዋጭ በነኝህ ዋስትናዎች ለአነስተኛ ንግድ እንዲሁም ለንግድ መኪና ያበድራል:- በቁጠባ ዋስትና፣ በደመወዝ ዋስትና እና በአባል ዋስትና፣ በንብረት ዋስትና (ለየመኪና እና የቤት ብድር የሚገዛው ንብረት ራሱ ዋስትና ይሆናል)

 

የአዋጭ የዋና መሥሪያ ቤት፣ የቅርንጫፎች አድራሻ እና ስልክ ቁጥሮች

ቅርንጫፍአድራሻስልክ ቁጥር
ዋና መሥሪያ ቤትአዲስ አበባ፣ አዋሬ አጋር ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 11 557 97 98
ዋና መሥሪያ ቤትአዲስ አበባ፣ አዋሬ አጋር ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 11 557 88 89
ዋና መሥሪያ ቤትአዲስ አበባ፣ አዋሬ አጋር ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 11 557 98 99
ዋና መሥሪያ ቤትአዲስ አበባ፣ አዋሬ አጋር ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 944 69 69 69
ቅርንጫፍአድራሻስልክ ቁጥር
ሥላሴ ቅርንጫፍ
ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሕንፃ 1ኛ ፎቅ+251 111 26 01 92
ስታዲዮም ቅርንጫፍ
የሓ ሲቲ ሴንተር 1ኛ ፎቅ +251 118 12 44 13
ስድስትኪሎ ቅርንጫፍ
ሊደርሺፕ ሕንፃ ምድር ላይ+251 118 68 55 98
ልደታ ቅርንጫፍ
ኤ አይ ኤ የገበያ ማዕከል ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 115 30 30 98
ሰዓሊተ ምህረት ቅርንጫፍ ድራር ሞል 1ኛ ፎቅ
+251 116 73 2011
ጀሞ ቅርንጫፍ
ኤክስፕረስ ፕላዛ 1ኛ ፎቅ+251 113 69 86 83
አዲሱ ገበያ ቅርንጫፍ
ጃምቦ ሕንፃ 3ኛ ፎቅ+251 111 54 74 40
ቦሌ ቅርንጫፍ
ቦሌ መድኃኒዓለም ሽግር ህንፃ ፊት ለፊት ከንብ ባንክ አጠገብ ባለው ህንፃ 1ኛ ፎቅ+251116671443
ቃሊቲ ቅርንጫፍ
ቃሊቲ ቶታል ካፍደም ህንፃ 2ኛ ፎቅ+251114715955
ቅርንጫፍአድራሻስልክ ቁጥር
ቢሾፍቱ ቅርንጫፍጠንክርና ቤተሰቡ ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 118 12 42 42
ጫንጮ ቅርንጫፍ
አዳም ሕንፃ ምድር ላይ+251 118 12 43 44
ሰበታ ቅርንጫፍ
ሳምቡሳ ቤት አካባቢ ኦፍታና ህንፃ ፊትለፊት+251 113 38 45 23
ሆለታ ቅርንጫፍ
ቀልቤሳ ሆቴል አጠገብ ሃና ፋርማሲ ያለበት ህንፃ 1ኛ ፎቅ+251 112 61 07 77

ጠቃሚ መረጃዎች ስለ አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የሕብረት ሥራ ማኅበር

ተ.ቁ.የብድር ዓይነትየብድር መጠን በብር እስከብድር ለመውሰድ የቅድመ ቁጠባ መጠን በመቶኛ (%)ብድር ለመውሰድ የቅድመ ቁጠባ መጠን በብርብድር ለመውሰድ የቅድመ ቁጠባ መጠንና ጊዜ በተከታታይየብድር ወለድ መጠን በመቶኛ (%)የብድር መመለሻ ጊዜ እና ገደብ
1መደበኛ ብድር - ለማኅበራዊ ጉዳይ100,000 (አንድ መቶ ሺህ)25%25,000 (ሃያ አምስት ሺህ)6 ወር እና ከዚያ በላይ13.5%3 ዓመት
2መደበኛ ብድር - ለትምህርትና ለጤና 100,000 (አንድ መቶ ሺህ)25%25,000 (ሃያ አምስት ሺህ)6 ወር እና ከዚያ በላይ13.5%3 ዓመት
3መደበኛ ብድር - ለአነስተኛ ንግድ400,000 (አራት መቶ ሺህ)25%100,000 (አንድ መቶ ሺህ)6 ወር እና ከዚያ በላይ13.5%3 ዓመት
4ለቤት መኪና ብድር600,000 (ስድስት መቶ ሺህ)40%240,000 (ሁለት መቶ አርባ ሺህ)1 ዓመት እና ከዚያ በላይ14.5%5 ዓመት
5ለንግድ መኪና ብድር800,000 (ስምንት መቶ ሺህ)40%320,000 (ሦስት መቶ ሃያ ሺህ)1 ዓመት እና ከዚያ በላይ14.5%5 ዓመት
6ለቤት ብድር መያዣ መሥሪያ ማደሻ1,000,000 (አንድ ሚሊዮን)30%
300,000 (ሦስት መቶ ሺህ)1 ዓመት እና ከዚያ በላይ15.5%
10 ዓመት
አንድ አዲስ አባል የብድር አገልግሎት ለማግኘት ቢያንስ ለተከታታይ 6ወራት መቆጠብ ሲኖርበት ለመኪና እና ለቤት ብድር ደግሞ ቢያንስ አንድ ዓመት መቆጠብ አለበት በተጨማሪም የገቢ መግለጫ፣ተመጣጣኝ ዋስትና እና የጋብቻን ሁኔታ የሚገልፅ ሰርተፍኬት የራሱም የዋሱንም፣ ባል ወይም ሚስት በአካል ማቅረብ እንዲሁም ዋስም በአካል መቅረብ ይኖርበታል። ተበዳሪው ከጠቅላላ ብድሩ 1% የብድር መድህን እና 1% ደግሞ የአገልግሎት ክፍያ መክፈል አለበት።
  • በቁጠባ ዋስትና
  • በደመወዝ ዋስትና እና በአባል ዋስትና
  • በንብረት ዋስትና የሚሰጥ ብድር
  • የመኪና ብድር እና የቤት ብድር የሚገዛው ንብረት ራሱ ዋስትና ይሆናል።
  • ማንኛውም ብድር የሚሰጠው የተበዳሪው የመክፈል አቅም ያገናዘበና ባቀረበው ዋስትና መጠን ብቻ ነው።
  • የማኅበሩ መነሻ ወይም ዝቅተኛ መደበኛ ቁጠባ መጠን ብር 350.00 (ሦስት መቶ ሃምሳ) ወይም ከ30 ቀናት ገቢ ውስጥ 10% ሲሆን ይህን ቁጠባ ሳያቋርጥ በየወሩ መቆጠብ ይኖርበታል፣
  • እያንዳንዱ አባል ከመነሻ የቁጠባ መጠን በተጨማሪ የፍላጎት ቁጠባ መቆጠብ ይችላል።
  • አንድ አባል የቆጠበውን መደበኛ ቁጠባ ከአባልነት ሲለቅ ብቻ ይወስዳል። ነገር ግን ተጨማሪ/የፍላጎት ቁጠባውን አስገዳጅ በሆነ ጊዜ ወጪ አድርጎ መጠቀም ይችላል።
አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የህብረት ሥራ ማኅበር ህብረተሰቡ ከሚያገኘው ገቢ ላይ የተወሰነ ገንዘብ በመቆጠብ እራሱን በራሱ እንዲረዳና የቁጠባን ባህል በማዳበር ፈጣን የሆነ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ በአቶ ዘሪሁን ሸለመ ዋና መስራችነት 41አባላትን በማሰባሰብ መጋቢት 13/1999 ዓ.ም. በመጀመሪያ በአራዳ ክፍለ ከተማ በአዋጅ 147/91 ተመሠረተ። ኅብረት ሥራ ማኅበሩ ባሳየው ከፍተኛ እድገት የሥራ ክልሉን በማስፋት በፌዴራል ኅብረት ሥራ ኤጀንሲ ምዝገባ ቁጥር አገ/ቁ/ብ/005/09 ተመዝግቦ ፈቃድ ያለው፤ በፌደራል ኅብረት ሥራ ኤጀንሲ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ብቃት ማረጋገጫ መመሪያ ቁጥር 018/2007 መሠረት ተመዝኖ 81.65 ከመቶ በማግኘት በከፍተኛ ደረጃ የብቃት ማረጋገጫ እና የዕውቅና ምስክር ወረቀት ታህሳስ 26 ቀን 2009 ዓ.ም. የተሰጠው ኅ/ሥ/ማኅበር ነው። በተጨማሪም አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዓለም አቀፍ ኅብረት ሥራ ኅብረት (CA) አባል እንዲሁም የአፍሪካ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ኮንፌደሬሽን (ACCOSCA) ተባባሪ አባል የሆነ ማህበረሰብ አቀፍ ህብረት ሥራ ማኅበር ነው።
  • መደበኛ ቁጠባ
  • የፍላጎት ቁጠባ
  • የልጆች ቁጠባ
  • የቤት ቁጠባ
  • የመኪና ቁጠባ
  • የጊዜ ገደብ ቁጠባ
  • በተመጣጣኝ ወለድ የብድር አገልግሎት መስጠት
  • አነስተኛ የብድር መድህን አገልግሎት
  • የትምህርት፣ ሥልጠና እና ማማከር አገልግሎት
  • የአዋጭ በሕብረት ሥራ ማኅበሩ የሥራ ክልል ነዋሪ የሆነና የነዋሪነት ማረጋገጫ ያለው
  • ዕድሜው 18 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆነ
  • የሕብረት ሥራ ማኅበሩ አባል በመሆን በኅብረት ሠርቶ በኅብረት ለማደግ ዓላማ ያለው
  • በሕብረት ሥራ ማኅበሩ ደንብና መመሪያ ተገዢ ለመሆን ፈቃደኛ የሆነ/ነች
  • በሕግ መብቱ ያልተገፈፈ
  • አንድ አመልካች አባል እንዲሆን ሲፈቀድለት የመመዝገቢያ ለአንድ ጊዜ ብቻ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ የተወሰነውን የገንዘብ መጠን ይከፍላል።
  • ለመመዝገቢያ የተከፈለ ገንዘብ በስንብት ወቅት ለአባላት ተመላሽ አይሆንም።
  • የአንድ ዕጣ ዋጋ ብር 1,000.00 ሲሆን አንድ አባል መግዛት ያለበት ዝቅተኛው የዕጣ መጠን ሁለት ነው።
  • አንድ አባል በጠቅላላ ጉባዔ ተወካይ አባላት እንዲሸጥ ከተወሰነው የዕጣ መጠን ከ10 በመቶ በላይ ድርሻ ሊኖረው አይችልም።
  • በሕ/ሥ/ማኅበሩ የዕጣ እና ቁጠባ ምጥጥን መሰረት አንድ አባል በየጊዜው 1፡3.5 መሰረት ዕጣ መግዛት ይጠበቅበታል።

ማስታወሻ፦ ይሄ መረጃ የተዘጋጀው አዋጭ በሚያዘጋጀው ብሮሹር እና በአካል ሄዶ በመጠየቅ በተገኘው መረጃ ላይ ተመሥርቶ ለጥቃቅን እና አነስተኛ ድርጅቶች በሚጠቅም መልኩ ተቀናብሮ ነው።

ይህንንም ይመልከቱ

ግሬት የገንዘብ ቁጠባና ብድር

ግሬት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር ማኅበረ ሰቡ ከሚያገኘው ገቢ ላይ በመቆጠብ …