መነሻ / ፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት / የግል ብድር እና ቁጠባ ተቋማት / አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የህብረት ሥራ ማኅበር

አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የህብረት ሥራ ማኅበር

አዋጭ ለአነስተኛ የንግድ ሥራ እስከ ብር 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ድረስ የሚያበድር ሲሆን ለንግድ መኪና ደግሞ እስከ ብር 2አዋጭ ለአነስተኛ የንግድ ሥራ እስከ ብር 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ድረስ የሚያበድር ሲሆን ለንግድ መኪና ደግሞ እስከ ብር 2,000,000 (ሁለት ሚሊዮን) ድረስ ያበድራል።

ለመበደር ምን ማድረግ አለብኝ?

ለአነስተኛ ንግድ ሥራ ብድር አባል ሆኖ ቢያንስ ለ6 (ስድስት) ወራት በተከታታይ መቆጠብ ይኖርበታል። የሚበደረውን ገንዘብ መጠን 25% (አንድ አራተኛ) መቆጠብ አለበት።

የንግድ መኪና ለመግዛት ለሚሰጥ ብድር አባል ሆኖ ቢያንስ ለ 6 (ስድስት) ወራት በተከታታይ መቆጠብ ይኖርበታል ። የሚበደረውን ገንዘብ መጠን 25% (ሃያ አምስት ፕርሰንት) መቆጠብ አለበት።

አዋጭ በነኝህ ዋስትናዎች ለአነስተኛ ንግድ እንዲሁም ለንግድ መኪና ያበድራል:- በቁጠባ ዋስትና፣ በደመወዝ ዋስትና እና በአባል ዋስትና፣ በንብረት ዋስትና (ለየመኪና እና የቤት ብድር የሚገዛው ንብረት ራሱ ዋስትና ይሆናል)

የአዋጭ የዋና መሥሪያ ቤት፣ የቅርንጫፎች አድራሻ እና ስልክ ቁጥሮች

ቅርንጫፍአድራሻስልክ ቁጥር
ዋና መሥሪያ ቤትአዲስ አበባ፣ አዋሬ አጋር ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 11 557 97 98
ዋና መሥሪያ ቤትአዲስ አበባ፣ አዋሬ አጋር ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 11 557 88 89
ዋና መሥሪያ ቤትአዲስ አበባ፣ አዋሬ አጋር ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 11 557 98 99
ቅርንጫፍአድራሻስልክ ቁጥር
አብይ ቅርንጫፍ ሜክሲኮ ህብረት ባንክ ዋና መ/ቤት+251 11 126 05 06
ሥላሴ ቅርንጫፍ
ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሕንፃ 1ኛ ፎቅ+251 111 26 01 92
ስታዲዮም ቅርንጫፍ
የሓ ሲቲ ሴንተር 1ኛ ፎቅ +251 115 58 25 55
ስድስትኪሎ ቅርንጫፍ
ሊደርሺፕ ሕንፃ ምድር ላይ+251 118 68 55 98
ልደታ ቅርንጫፍ
ኤ አይ ኤ የገበያ ማዕከል ሕንፃ 2ኛ ፎቅ+251 115 30 30 98
ሰዓሊተ ምህረት ቅርንጫፍ ድራር ሞል 1ኛ ፎቅ
+251 116 73 2011
ጀሞ ቅርንጫፍ
ኤክስፕረስ ፕላዛ 1ኛ ፎቅ+251 113 69 86 83
አዲሱ ገበያ ቅርንጫፍ
ጃምቦ ሕንፃ 3ኛ ፎቅ+251 111 54 74 40
ቦሌ ቅርንጫፍ
ቦሌ መድኃኒዓለም ሸገር ህንፃ ፊት ለፊት አስረስ ህንፃ 1ኛ ፎቅ+251 116 67 19 23
ቃሊቲ ቅርንጫፍ
ቃሊቲ ቶታል ካፍደም ህንፃ 2ኛ ፎቅ+251114715955
መገናኛ ቅርንጫፍ መሰረት ደፋር ሕንፃ ምድር+251 116 68 66 53
ቅርንጫፍአድራሻስልክ ቁጥር
ቢሾፍቱ ቅርንጫፍቱሪስት ሰፈር ፣ ሚና ቤና ሕንፃ 1ኛ ፎቅ+251 118 12 42 42
ጫንጮ ቅርንጫፍ
አዳም ሕንፃ ምድር ላይ+251 118 12 43 44
ሰበታ ቅርንጫፍ
ሳምቡሳ ቤት አካባቢ ኦፍታና ህንፃ ፊትለፊት+251 113 38 45 23
ሆለታ ቅርንጫፍ
ቀልቤሳ ሆቴል አጠገብ ሃና ፋርማሲ ያለበት ህንፃ 1ኛ ፎቅ+251 112 61 07 77
አዳማ ቅርንጫፍዋርካ ፊት ለፊት ኪዳነ ምህረት ሥጋ ቤት አጠገበ ኤ.ኤች.ዋይ ሆቴል 2ኛ ፎቅ+251 222 12 00 88/89
ቅርንጫፍአድራሻስልክ ቁጥር
ሐዋሳ ቅርንጫፍአሮጌው መናኸሪያ ትዕግስት ሆቴል አጠገብ 1ኛ ፎቅ+251 462 12 24/26

ጠቃሚ መረጃዎች ስለ አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የሕብረት ሥራ ማኅበር

አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የህብረት ሥራ ማኅበር ህብረተሰቡ ከሚያገኘው ገቢ ላይ የተወሰነ ገንዘብ በመቆጠብ እራሱን በራሱ እንዲረዳና የቁጠባን ባህል በማዳበር ፈጣን የሆነ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ በአቶ ዘሪሁን ሸለመ ዋና መስራችነት 41አባላትን በማሰባሰብ መጋቢት 13/1999 ዓ.ም. በመጀመሪያ በአራዳ ክፍለ ከተማ በአዋጅ 147/91 ተመሠረተ። ኅብረት ሥራ ማኅበሩ ባሳየው ከፍተኛ እድገት የሥራ ክልሉን በማስፋት በፌዴራል ኅብረት ሥራ ኤጀንሲ ምዝገባ ቁጥር አገ/ቁ/ብ/005/09 ተመዝግቦ ፈቃድ ያለው፤ በፌደራል ኅብረት ሥራ ኤጀንሲ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ብቃት ማረጋገጫ መመሪያ ቁጥር 018/2007 መሠረት ተመዝኖ 81.65 ከመቶ በማግኘት በከፍተኛ ደረጃ የብቃት ማረጋገጫ እና የዕውቅና ምስክር ወረቀት ታህሳስ 26 ቀን 2009 ዓ.ም. የተሰጠው ኅ/ሥ/ማኅበር ነው። በተጨማሪም አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዓለም አቀፍ ኅብረት ሥራ ኅብረት (CA) አባል እንዲሁም የአፍሪካ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ኮንፌደሬሽን (ACCOSCA) ተባባሪ አባል የሆነ ማህበረሰብ አቀፍ ህብረት ሥራ ማኅበር ነው።

ራዕይ

በ2030 ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ኀብረት ሥራ ማኀበር ሆኖ ማየት

ተልዕኮ

አባላት በማስተባበር ተገቢውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በፍላጎት ላይ የተመሠረተ በሀገራችን የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ላይ አስተዋፅኦ በማበርከት የተሻለ የቁጠባ፣ ብድር እና ሌሎች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኙ በማድረግ የኑሮ ደረጃቸውን ማሻሻል።

ዓላማ

  • ዘላቂነት ያለው የገንዘብ ተቋም በመፍጠር ባንክ ነክ አገልግሎት ለአባላት በመስጠት የገቢ መጠናቸውን ማሳደግ እና የደህነት መጠንን መቀነስ
  • የተለየ እገዛ የሚፈልጉ ሴቶችን እና ወጣቶችን እንዲሁም አካል ጉዳተኞችን በማበረታታት በገቢ ማስገና ሥራ ላይ ተሰማርተው ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ ማበረታታት እና ድጋፍ ማድረግ
  • በሀገራችን መንግሥት ባስቀመጠው የልማት ዕቅዶች ላይ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ
  • ለአባላት፣ አመራር፣ አቅጥር ሠራተኛ እና ለህብረተሰቡ ተከታታይ ሥልጠና እና ትምህርት በመስጠት በኅብረት ሥራ ማህበሩ የሚያደርጉትን ተሳትፎ ማሳደግ
  • ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለአባላት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የአገልግሎቱ ተደራሽነት ማስፋት
ተ.ቁ.የብድር ዓይነትየብድር መጠን በብር እስከብድር ለመውሰድ የቅድመ ቁጠባ መጠን በመቶኛ (%)ብድር ለመውሰድ የቅድመ ቁጠባ መጠን በብርብድር ለመውሰድ የቅድመ ቁጠባ መጠንና ጊዜ በተከታታይየብድር ወለድ መጠን በመቶኛ (%)የብድር መመለሻ ጊዜ እና ገደብ
1መደበኛ ብድር - ለማኅበራዊ ጉዳይ600,000 (ስድስት መቶ ሺህ)25%150,000 (መቶ ሃምሳ ሺህ)6 ወር እና ከዚያ በላይ13.5%3 ዓመት
2መደበኛ ብድር - ለአነስተኛ ንግድ800,000 (ስምንት መቶ ሺህ)25%200,000 (ሁለት መቶ ሺህ)6 ወር እና ከዚያ በላይ13.5%3 ዓመት
3ለቤት መኪና ብድር1,500,000 (አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን)25%375,000 (ሦስት መቶ ሰባ አምስት ሺህ)6 ወር እና ከዚያ በላይ14.5%5 ዓመት
4ለንግድ መኪና ብድር2,000,000 (ሁለት ሚሊዮን)25%500,000 (አምስት መቶ ሺህ)6 ወር እና ከዚያ በላይ14.5%5 ዓመት
5ለቤት ብድር መያዣ መሥሪያ ማደሻ3,000,000 (ሦስት ሚሊዮን)25%
750,000 (ሰባት መቶ ሃምሳ ሺህ)6 ወር እና ከዚያ በላይ15.5%
10 ዓመት
አንድ አዲስ አባል የብድር አገልግሎት ለማግኘት ቢያንስ ለተከታታይ 6ወራት መቆጠብ አለበት። ብድር ከመጠየቁ ከአንድ ወር በፊት ተበዳሪው የጠየቀውን የብድሩን መጠን ከሚፈለገው 25 በመቶ የቁጠባ መጠን ውስጥ 75 በመቶ የሚሆነው የቁጠባ መጠን እና ከዚያ በላይ የሚሆነውን ለሁለት ወይም ከዚያ በላይ ለተከታታይ ወራት ወይም በየወሩ ለተከታታይ ስድስት ወር ወይም ከዚያ በላይ የቆጠበ እና ቀሪውን 25 በመቶ እና በቻት የሆነውን የቁጠባ መጠን በስድስተኛ ወር ወይም ከዚያ በላይ ባሉ ወራት አጠናቆ የቆጠበ።
  • በቁጠባ ዋስትና
  • በደመወዝ ዋስትና እና በአባል ዋስትና
  • በንብረት ዋስትና የሚሰጥ ብድር
  • የመኪና ብድር እና የቤት ብድር የሚገዛው ንብረት ራሱ ዋስትና ይሆናል።
  • ማንኛውም ብድር የሚሰጠው የተበዳሪው የመክፈል አቅም ያገናዘበና ባቀረበው ዋስትና መጠን ብቻ ነው።
  • የባንክ ወይም የኢንሹራንስ አክሲዮን
  • የማኅበሩ መነሻ ወይም ዝቅተኛ መደበኛ ቁጠባ መጠን ብር 500 (አምስት መቶ) ወይም ከ30 ቀናት ገቢ ውስጥ 10% ሲሆን ይህን ቁጠባ ሳያቋርጥ በየወሩ መቆጠብ ይኖርበታል፣
  • እያንዳንዱ አባል ከመነሻ የቁጠባ መጠን በተጨማሪ የፍላጎት ቁጠባ መቆጠብ ይችላል።
  • አንድ አባል የቆጠበውን መደበኛ ቁጠባ ከአባልነት ሲለቅ ብቻ ይወስዳል። ነገር ግን ተጨማሪ/የፍላጎት ቁጠባውን አስገዳጅ በሆነ ጊዜ ወጪ አድርጎ መጠቀም ይችላል።

የቁጠባ አገልግሎት

  • መደበኛ ቁጠባ
  • የፍላጎት ቁጠባ
  • የልጆች ቁጠባ
  • የቤት ቁጠባ
  • የመኪና ቁጠባ
  • የጊዜ ገደብ ቁጠባ
  • በተመጣጣኝ ወለድ የብድር አገልግሎት መስጠት
  • አነስተኛ የብድር መድህን አገልግሎት
  • የትምህርት፣ ሥልጠና እና ማማከር አገልግሎት

የብድር አገልግሎት

  • መደበኛ ብድር
  • የንግድ ሥራ ማስጀመሪያ እና ማስፋፊያ ብድር
  • የቤት መግዣ፣ መስሪያና ማደሻ ብድር
  • ለንግድ አገልግሎት የሚውል ተሽከርካሪ ብድር
  • ለግል አገልግሎት የሚውል ተሽከርካሪ ብድር

በተጨማሪ ደግሞ

  1. አነስተኛ የብድር መድህን አገልግሎት
  2. የትምህርት፣ ሥልጠና እና ማማከር አገልግሎት ናቸው
  • የአዋጭ በሕብረት ሥራ ማኅበሩ የሥራ ክልል ነዋሪ የሆነና የነዋሪነት ማረጋገጫ ያለው
  • ዕድሜው 18 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆነ
  • የሕብረት ሥራ ማኅበሩ አባል በመሆን በኅብረት ሠርቶ በኅብረት ለማደግ ዓላማ ያለው
  • በሕብረት ሥራ ማኅበሩ ደንብና መመሪያ ተገዢ ለመሆን ፈቃደኛ የሆነ/ነች
  • በሕግ መብቱ ያልተገፈፈ
  • የታደሰ የቀበሌ ነዋሪነት መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም መንጃፈቃድ ማቅረብ የሚችል
  • አንድ አመልካች አባል እንዲሆን ሲፈቀድለት የመመዝገቢያ ለአንድ ጊዜ ብቻ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ የተወሰነውን የገንዘብ መጠን ይከፍላል።
  • ለመመዝገቢያ የተከፈለ ገንዘብ በስንብት ወቅት ለአባላት ተመላሽ አይሆንም።
  • የአባሉ ቁጠባ እና እጣ መጠን
  • የኅብረት ሥራ ማህበር አባል የሆነ ለዋስትናነት
  • ለዋስትናነት የቀረበ የቋሚ ቅጥር ሰራተኛ ደመወዝ ህጋዊ ደብዳቤ
  • የንብረት ዋስትና ካርታ ወይም ሊብሬ
  • የንብረት እግድ አግባብ ካለው አካል ጋር የቀረበ ማረጋገጫ
  • በህጋዊ አካል የቀረበ የአክሲዮን ሰነድ ለዋስትናነት
  • ያላገባ ወይም ያገባ ስለመሆኑ የሚገልጽ የጋብቻ ሰርተፍኬት
  • የተበዳሪው እና የተበዳሪ ባለቤት፣ ዋስ የሆነ ግለሰብ እና የሚስት/ የባል የታደሰ የቀበሌነት መታወቂያ
  • በተበዳሪ የተፈረመ ገቢያቸውን የሚገልጽ ዝርዝር መግለጫ
  • የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ ቁጥር እና የዘመኑ ግብር የተከፈከ ማረጋገጫ
  • የንግድ እንቅስቃሴያቸውን የሚገልጽ የንግድ ሥራ እቅድ ወይም መግለጫ
  • የአንድ ዕጣ ዋጋ ብር 1,000.00 ሲሆን አንድ አባል መግዛት ያለበት ዝቅተኛው የዕጣ መጠን ሁለት ነው።
  • አንድ አባል በጠቅላላ ጉባዔ ተወካይ አባላት እንዲሸጥ ከተወሰነው የዕጣ መጠን ከ10 በመቶ በላይ ድርሻ ሊኖረው አይችልም።
  • በሕ/ሥ/ማኅበሩ የዕጣ እና ቁጠባ ምጥጥን ሥራ ይከናወናል

ማስታወሻ፦ ይሄ መረጃ የተዘጋጀው አዋጭ በሚያዘጋጀው ብሮሹር እና በአካል ሄዶ በመጠየቅ በተገኘው መረጃ ላይ ተመሥርቶ ለጥቃቅን እና አነስተኛ ድርጅቶች በሚጠቅም መልኩ ተቀናብሮ ነው።

ይህንንም ይመልከቱ

ኒኦ አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ.

ኒኦ አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ. ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባገኘው ፈቃድ መሠረት በተለያዩ የንግድ ዘርፎች ላይ …