መነሻ / የጥቃቅን እና አነስተኛ መረጃ / ወቅታዊ መረጃ / በኮሮና ቫይረስ ለተጎዱ ኢንተርፕራይዞች የቀረበ ዝቅተኛ ወለድ እና እፎይታ ያለው ብድር

በኮሮና ቫይረስ ለተጎዱ ኢንተርፕራይዞች የቀረበ ዝቅተኛ ወለድ እና እፎይታ ያለው ብድር

በኮሮና ቫይረስ ወረሽኝ የተነሣ በደረሰው የንግድ መቀዛቀዝ ውስጥ፣ ሥራቸውን ለመቀጠል እየጣሩ ያሉ ጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ለመደገፍ የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን፣ ማስተርካርድ ፋውንዴሽን እና ፈርስት ኮንሰልት በጋራ ኢንተርፕራይዞቹ ድጋፍ የሚያገኙበት ፕሮጀክት አዘጋጅተዋል።

በፕሮጀክቱም መስፈርቱን የሚያሟሉ ኢንተርፕራይዞች ዝቅተኛ ወለድ እና የእፎይታ ጊዜ ያለው ብድር ተመቻችቶላቸዋል።

በዚህም መሠረት፡-

የሠራተኞች ብዛት፡- ከ 2 እስከ 5 ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ፣ ከ 6 እስከ 30 ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ
እስከ ሰኔ 2012 ዓ.ም ድረስ ቢያንስ አንድ ዓመት ሥራ ላይ የቆየ

በተለይ፣ በሴቶች እና በወጣቶች ለሚተዳደሩ ኢንተርፕራይዞች ፕሮጀክቱ ቅድሚያ እንደሚሰጥም ተገልጿል።

መስፈርቱን የምታሟሉ ኢንተርፕራይዞች፣ ወይም ዝርዝሩን ለመመልከት ይህንን ሊንክ ይከተሉ፡-

https://www.ethiomsefund.com/landing/home/info

ይህንንም ይመልከቱ

TUC_NSP_2merkato_poster_ad_20221031-04

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የ4 ሳምንት የሙያ ክህሎት ሥልጠናዎች

በኮንስትራክሽን ዘርፍ ለተሰማራችሁ ኢንተርፕራይዞች ከቤት እስከ ከተማ የከተማ ማዕከል (The Urban Center) የ4 ሳምንት የሙያ …