መነሻ / የጥቃቅን እና አነስተኛ መረጃ / ወቅታዊ መረጃ / የሲሚንቶ ዋጋ ተመን እና ቁጥጥር በአዲስ አበባ
cement-bag

የሲሚንቶ ዋጋ ተመን እና ቁጥጥር በአዲስ አበባ

መንግስት ካስቀመጠው የሲሚንቶ ዋጋ በላይ በሚሸጡ የሲሚንቶ አከፋፋዮች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ አስታወቀ ፡፡

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በሲሚንቶ ግብይት ውስጥ ያሉ ህገ-ወጥ ደላሎችን ከገበያ ሰንሰለቱ በማስወጣት እየናረ የመጣውን የሲሚንቶ ዋጋ ለማስተካከል የመሸጫ ዋጋ በመተመን ከፋብሪካ አውጥተው የሚያከፋፍሉ የመንግስት የልማት ድርጅቶችና መመሪያውን አክብረው ለመስራት የተስማሙ የግል ነጋዴዎች ተመርጠው በቅርቡ ወደ ስራ መግባታቸው ይታወሳል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮው አላስፈላጊ የሲሚንቶ ዋጋ ንረትን በመቆጣጠርና ዋጋ በመተመን የኮንስትራክሽን ዘርፉ እንዳይዳከም በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

ከፋብሪካዎች ተረክበው የሚሸጡ አከፋፋዮች የሚሸጡበት የአንድ ኩንታል ዋጋ እንደየርቀቱ ከ240.20 ብር እስከ 388.10 ብር እንዲሆን የተወሰነ ቢሆንም አንዳንድ አከፋፋዮች ግን ከተቀመጠው ዋጋ በላይ በመሸጥ ላይ እንደሚገኙ በተደረገ የመስክ ምልከታ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡

መንግስት ባስቀመጠው የሲሚንቶ ዋጋ መሰረት ግብይት በማይፈጽሙ የሲሚንቶ አከፋፋዮች ላይ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወሰድ ቢሮው ገልጿል፡፡

addis_ababa_cement

ምንጭ (የዜና እና የሲሚንቶ ዋጋ ተመን ምስል)፦ የአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬታሪ ቢሮ የፌስቡክ ገጽ

ይህንንም ይመልከቱ

kefta-care-training-2

ከፍታ ለ20 ኢንተርፕራይዞች ሥልጠና ሰጠ

ከፍታ ከኬር ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለ20 በሴቶች ለሚተዳደሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሥልጠና ሰጠ። ሥልጠናው ያተኮረው …