ጎኅ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር በኅዳር 6 ቀን፣ 2014 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር የኅብረት ሥራ ኤጀንሲ ማኅበራት ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 985/2009 ዓ.ም. አንቀጽ 10 መሠረት ጎኅ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር በግ ታውቆ በመዝገብ ቁጥር አራ/1/1/750/2014 ዓ.ም ተመዝግቦ የተቋቋመ ነው።
ተጨማሪTag Archives: microfinance
በጋራ እንችላለን – ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር የቁጠባ ባሕልን ለማሳደግ፣ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ አሁን ከደረሰበት ደረጃ ጋር በተያያዘ በኢኮኖሚው ዘርፍ ጠንካራ ተዋናይ ሆኖ ለመገኘት የሚያስፈልገውን የፋይናንስ ፍላጎት በጋራ ሆኖ ለማሟላት፣ እንዲሁም የገንዘብ አጠቃቀምና አስተዳደር ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ዓላማ ባደረጉ የኅብረተ ሰብ ክፍሎች የተቋቋመ የኅብረት ሥራ ማኅበር ነው። ማኅበሩ በ2009 …
ተጨማሪአዲስ ራፋይሰን የኅብረት ሥራ ሠራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር
አዲስ ራፋይሰን የኅብረት ሥራ ሠራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር በ2003 ዓ.ም. በኅብረት ሥራ ሠራተኞችና ባለሙያዎች የተቋቋመ የኅብረት ሥራ የፋይናንስ ተቋም ነው። የኅብረት ሥራ ማኅበሩ የኅብረት ሥራ ባለሙያዎችና ሠራተኞችን በአባልነት በማቀፍ በዚህ ዘርፍ የተሻለ አስተዋፅኦ ለማበርከት የተቋቋመ ማኅበር ነው። ስሙን የወሰደው ከ Friedrich Wilhelm Raiffeisen ሲሆን፤ ራፋይሰን …
ተጨማሪማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት 5.5 ቢሊዮን ብር ከአዋሽ ባንክ በብድር ሊያገኙ ነው
አዋሽ ባንክ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ውስጥ ለተለያዩ የማክሮ ፋይናንስ ተቋማት 5.5 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ። ባንኩ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ለማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት (ለአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት) ለማበደር ካቀደው በጀት ውስጥ 1.5 ቢሊዮን ብር የሚሆነውን ብድር ተጠቃሚ ከሚሆኑ ዘጠኝ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ጋር ባለፈው ሐሙስ ሐምሌ 21 ቀን …
ተጨማሪ“ዛሬ በመቆጠብ ነገን በተሻለ ህይወት ይኑሩ” – አፍሪካ ቪሌጅ ፋይናንሽያል ሰርቪስስ አ.ማ.
አፍሪካ ቪሌጅ ፋይናንሽያል ሰርቪስስ አ.ማ. በአዋጅ ቁጥር 626/2009 መሠረት ተቋቁሞ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በማግኝት እ.ኤ.አ. ከ1999 ጀምሮ በኦሮሚያና በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ውስጥ ፋይናንስ ነክ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ የሚገኝ የፋይናንስ ተቋም ነው።
ተጨማሪድባብ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር
ድባብ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር ሁሉንም በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ነዋሪዎችን አባል ለማድረግ ዓላማ ይዞ የተቋቋመ የኅብረት ሥራ ማኅበር የፋይናንስ ተቋም ነው።
ተጨማሪሃበሻ ኢንተርፕረነርስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ ኅብረት ሥራ ማኅበር
ሃበሻ ኢንተርፕረነርስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ ኅብረት ሥራ ማኅበር የኅብረት ሥራ ማኅበራትን ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 985/09 መሠረት የተቋቋመ ሕጋዊ ድርጅት ነው። የሥራ ፈጣሪዎች በአንድነት የጋራ የሆኑ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ችግሮቻቸውን ለመፍታት እንዲችሉም የተቋቋመ ማሕበር ነው፡፡
ተጨማሪግሎባል የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/የኅብረት ሥራ ማኅበር
ግሎባል የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/የኅብረት ሥራ ማኅበር በአዋጅ 985/2009 እና ይህን አዋጅ ለማስፈጸም በወጡ ደንቦች መሠረት የተቋቋመት የኅብረት ሥራ ማኅበር ነው።
ተጨማሪኑ ነገን ዛሬ እንሥራ – ፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር
ፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር ኅብረተ ሰቡ ከሚያገኘው ገቢ ላይ የተወሰነ ገንዘብ በመቆጠብ ራሱን በራሱ እንዲረዳና የቁጠባ ባህልን በማዳበር ፈጣን የሆነ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ በ379 መስራች አባላት (307 ወንድ እና 72 ሴት) መጋቢት 15 ቀን፣ 2011 ዓ.ም. በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ተመሠረተ።
ተጨማሪጆሽዋ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/ የኅብረት ሥራ ማኅበር
ጆሽዋ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/ የኅብረት ሥራ ማኅበር በ1993 ዓ.ም ተመሥርቶ በብድር እና ቁጠባ ዘርፍ እየሠራ ያለ ማኅበር ነው። ከ24,000 በላይ አባላት እና ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ሀብት አለው። በቦሌ ደምበል (ኦሎምፒያ) አካባቢ በ1083 ካሬ ሜትር ላይ ባለ 4 ፎቅ ሕንጻ እና ለቢሮ ምቹ የሆኑ ተጨማሪ ክፍሎች ያሉት ግቢ …
ተጨማሪ