“የኛ ሁሌም የኛ የሁላችንም ነው!!” በሚል መሪ ቃል የሚታወቀው የኛ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሚገኙ እና በትምህርት ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆኑትን፣ እንዲሁም መካከለኛውን የኅብረተ ሰብ ክፍሎች በገንዘብ አስተዳደር እና አጠቃቀም እና በተለያዩ ሥልጠናዎች በማገዝ የኑሮና አኗኗር ለውጥን ለማምጣት እና ለመሥራት የተቋቋመ የገንዘብ ቁጠባና …
ተጨማሪTag Archives: አዲስ አበባ
አልአዛር እና ሄኖክ እንጨት እና ብረታ ብረት ሥራ
ድርጅቱ የተመሠረተው በአቶ አልአዛር ዓለም እና በአቶ ሄኖክ በ1996 ዓ.ም. ነው። ድርጅቱ አጠቃላይ የእንጨት እና የብረታ ብረት ሥራዎችን የሚሠራ ድርጅት ሲሆን በነዚህ ሥራዎች ውስጥ ውስጥ የዲዛይን እና ፈኒቸር ሥራዎች ይካተታሉ።
ተጨማሪፋና የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበር
ፋና የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበር በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ መሥራች አባላት ሐምሌ 13 ቀን፣ 2011 ዓ.ም. በሕጋዊ መንገድ ተመሠረተ።
ተጨማሪድባብ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር
ድባብ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር ሁሉንም በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ነዋሪዎችን አባል ለማድረግ ዓላማ ይዞ የተቋቋመ የኅብረት ሥራ ማኅበር የፋይናንስ ተቋም ነው።
ተጨማሪእቴጌ ዳቦ እና ብስኩት
ድርጅቱ የተመሠረተው በአቶ ሳሙኤል በለጠ፣ በሁለት ሴቶች እና አንድ ወንድ መሥራች አባላት በ2010 ዓ.ም. ነው። ይህ ድርጅት የሚያመርታቸው ምርቶች ምግብ እና መጠጥ ሲሆኑ በአሁን ጊዜ በዳቦ፣ ኩኪስ እና ጨው ምርቶች ላይ በስፋት እየሠራ ይገኛል።
ተጨማሪታሪክ ዲተርጀንት
ድርጅቱ የተመሠረተው በ2012 ዓ.ም. በወ/ሮ የምሥራች የምሩ እና አራት መሥራች አባላት ነው። ድርጅቱ አጠቃላይ ለንጽህና መጠበቂያ የሚያገለግሉ ፈሳሽ ሳሙናዎችን በጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ አምርቶ ለገበያ ያቀርባል።
ተጨማሪግሎባል የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/የኅብረት ሥራ ማኅበር
ግሎባል የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/የኅብረት ሥራ ማኅበር በአዋጅ 985/2009 እና ይህን አዋጅ ለማስፈጸም በወጡ ደንቦች መሠረት የተቋቋመት የኅብረት ሥራ ማኅበር ነው።
ተጨማሪተዋበ እንጨት እና ብረታ ብረት ሥራ
ድርጅቱ የተመሠረተው በአቶ ተዋበ ምኔነህ በ2004 ዓ.ም. የግል ኢንተርፕራይዝ ሆኖ ነው። ይህ ድርጅት አጠቃላይ የእንጨት እና የብረታ ብረት ሥራዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ይሠራል።
ተጨማሪኑ ነገን ዛሬ እንሥራ – ፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር
ፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር ኅብረተ ሰቡ ከሚያገኘው ገቢ ላይ የተወሰነ ገንዘብ በመቆጠብ ራሱን በራሱ እንዲረዳና የቁጠባ ባህልን በማዳበር ፈጣን የሆነ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ በ379 መስራች አባላት (307 ወንድ እና 72 ሴት) መጋቢት 15 ቀን፣ 2011 ዓ.ም. በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ተመሠረተ።
ተጨማሪገነት ልብስ ስፌት
ድርጅቱ የተመሠረተው በ2011 ዓ.ም. በወ/ሮ ገነት የግል ኢንተርፕራይዝ ሆኖ ነው። ይህ ድርጅት የሚያመርታቸው ምርቶች ባህላዊ እና ዘመናዊ ልብሶችን ሲሆን በይበልጥ ደግሞ የሴቶች እና የህጻናት ባህላዊ ልብሶችን ከዘመናዊ ልብሶች ጋር በማጣመር ያመርታል።
ተጨማሪ