መነሻ / ፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት (page 4)

ፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት

ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተፕራይዞች ምዝገባ ከፈፀሙ በኋላ የፋይናንስ ድጋፍ የሚያገኙባቸውን አማራጮች በዚህ ክፍል ሥር ያገኛሉ።

እንዲሁም ከተለያዩ ኢንተርፕራይዞች ጋር በሽርክና መሥራት የሚፈልጉ ኢንቨስትሮች እና ኢንቨስተር የሚፈልጉ ኢንተርፕራይዞች ዝርዝር እዚህ ይኖራል።

ኑ ነገን ዛሬ እንሥራ – ፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር

finot-logo

ፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር ኅብረተ ሰቡ ከሚያገኘው ገቢ ላይ የተወሰነ ገንዘብ በመቆጠብ ራሱን በራሱ እንዲረዳና የቁጠባ ባህልን በማዳበር ፈጣን የሆነ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ በ379 መስራች አባላት (307 ወንድ እና 72 ሴት) መጋቢት 15 ቀን፣ 2011 ዓ.ም. በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ተመሠረተ።

ተጨማሪ

ጆሽዋ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/ የኅብረት ሥራ ማኅበር

saving

ጆሽዋ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/ የኅብረት ሥራ ማኅበር በ1993 ዓ.ም ተመሥርቶ በብድር እና ቁጠባ ዘርፍ እየሠራ ያለ ማኅበር ነው። ከ24,000 በላይ አባላት እና ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ሀብት አለው። በቦሌ ደምበል (ኦሎምፒያ) አካባቢ በ1083 ካሬ ሜትር ላይ ባለ 4 ፎቅ ሕንጻ እና ለቢሮ ምቹ የሆኑ ተጨማሪ ክፍሎች ያሉት ግቢ …

ተጨማሪ

ሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም

sheger-mfi-logo

ሸገር ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ. በብዙሃን የግል ባለሃብቶች እና በግል ኩባንያዎች የተቋቋመና በብሔራዊ ባንክ ፍቃድ ያገኘ፣ በፋይናንስ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ተሞክሮና እውቀት ባካበቱ የሥራ ኃላፊዎች የሚመራ አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም ነው። በአሁኑ ወቅት ቅርንጫፎቹን በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መቀመጫ በሆነችው ፊንፊኔ (አዲስ አበባ) እና በሌሎች በክልሉ በሚገኙ ከተሞች በማስፋፋት የኅብረተ ሰቡን …

ተጨማሪ

ፒስ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ.

peace-mfi-logo

ፒስ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ. በአነስተኛ ፋይናንስ ሥራ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1164/2012 እና አዋጅ ቁጥር 624/2001 መሠረት በተሰጠው ፈቃድ ቁጥር MIF/012/2014 እ.ኤ.አ ሐምሌ 1999 የተቋቋመ ሲሆን ቅድሚያ ለሴቶች የሚሰጥ የማይክሮ ፋይናንስ ኩባንያ ነው።

ተጨማሪ

አጋር ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ.

agar-microfinance

አጋር ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ. መጋቢት 9 ቀን፣ 1996 ዓ.ም.  ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕጋዊ የሥራ ፈቃድ አግኝቶ የባንክ የፋይናንስ  አገልግሎት ለማያገኙ የኅብረተ ሰብ ክፍሎች የቁጠባና የብድር አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ኩባንያ ነው። ተቋሙ ከተመሠረተ ከ17 ዓመታት በላይ በሥራው ላይ የቆየ ሲሆን አጥጋቢ የሥራ ልምድ ከማካበቱም በላይ በአሁኑ ወቅት ቅርጫፎቹን ወደ ሃያ …

ተጨማሪ

አሚጎስ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር

አሚጎስ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር የተቋቋመው በኢትዮጵያ የኅብረት ሥራ ማኅበር አዋጅ መሠረት በቁጥር 147/1998 ሲሆን ሕጋዊ ሰብእናውን  ከአራዳ ክፍለ ከተማ የኅብረት ሥራ ማኅበር ማደራጃ ቢሮ እና ከንግድ ሚኒስቴር በጥር 2005 ዓ.ም. ፍቃድ አግኝቶ በሥራ ላይ ይገኛል። አሚጎስ በቀዳሚነት የሚንቀሳቀሰው የአባላት መደበኛ ቁጠባ እና አክሲዮን በመሰብሰብ የተሻለ የብድር አገልግሎት በማቅረብ …

ተጨማሪ

አዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም

አዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም አክሲዮን ማኅበር በአዋጅ ቁጥር 40/1988 ዓ.ም. መሠረት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በማግኘት በስድስት የአክሲዮን ባለቤቶች የብድርና ቁጠባ አገልግሎት ለመስጠት እ.አ.አ ጥር 27 ቀን፣ 2000 ዓ.ም. በከተማው ያለውን ሥራ አጥነት ለመቅረፍና ድህነትን ለመቀነስ ዓላማ አድርጎ የተቋቋመ ተቋም ነው። በአሁን ሰዓት በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 626/2009 እየሠራ የሚገኝ እና …

ተጨማሪ

መክሊት የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም አ.ማ.

meklit-logo

መክሊት የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም አ.ማ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው አዋጅ ቁጥር 40/96 ከዚያም ተሻሽሎ በወጣው አዋጅ ቁጥር 626/2009 መሠረት በከተማና በገጠር ለሚኖሩ ምርታማ ዜጎች በተለይም የባንክ አገልግሎት ዕድል ላላገኙ ሴቶች እና ወጣቶች የብድር፤ የቁጠባና አነስተኛ የመድን ዋስትና አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመ ሲሆን ላለፉት 19 ዓመታት አገልግሎቱን በጥራትና በብቃት እያቀረበ የሚገኝ …

ተጨማሪ

ግራንድ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ.

ግራንድ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ. በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች በከተማና በገጠር የሚኖሩ ለሥራ ተነሻሽነት ያላቸው ዜጎች በተለይም የባንክ አገልግሎት ዕድል ለተነፈጉ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ነጋዴዎችና አርሶ አደሮች የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለመስጠት ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በማግኘት የተቋቋመ ተቋም ነው። ማስታወሻ፦ ይሄ መረጃ የተዘጋጀው ግራንድ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም በአካል ሄዶ በመጠየቅ በተገኘው መረጃ ላይ ተመሥርቶ …

ተጨማሪ

ሀርቡ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም

harbu-mfi

ሀርቡ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ. በ2005 ዓ.ም. በፋሲሊቴተር ፎር ቼንጅ (መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም) ድጋፍ አማካኝነት የተቋቋመ ተቋም ነው። ሀርቡ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ. የዕሴት ሰንሰለት ልማት እና የፋይናንስ አገልግሎቶችን ተደራሽነት በመደገፍ የግብርና ምርታማነትን እና የግብርና ግብይትን ለማሳደግ ያለመ ነው። ማስታወሻ፦ ይሄ መረጃ የተዘጋጀው ሀርቡ ማይክሮ ፋይናንስ በአካል ሄዶ በመጠየቅ በተገኘው …

ተጨማሪ