መነሻ / የቢዝነስ ዜና (page 4)

የቢዝነስ ዜና

በዚህ ስር የቢዝነስ ዜናዎች ይቀርባሉ።

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ የቆዳ ፋብሪካዎችን ጎበኙ

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እና የአግሮ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ ሚ/ዴኤታ አቶ ተካ ገ/የስ ትናንትና ነሐሴ 15 ቀን 2012 ዓ.ም በተለያዩ የቆዳ ፋብሪካዎች ተገኝተው የስራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ ለግማሽ ቀን በቆየው የስራ ጉብኝት ላይ የውጭ ምንዛሬ፣ የመሬት፣ የመብራት መቆራረጥ፣ የተማረ የሰው ኃይል፣የመስሪያ ካፒታል ችግሮች እንዳሉ በዘርፉ ተዋንያኖች የተጠቆመ ሲሆን እነዚህንና መሰል …

ተጨማሪ

አዲስ የአኩሪ አተር ፕሮቲንና ዘይት ፋብሪካ ሥራ ጀመረ

ሪችላንድ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር በቡሬ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከ991 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የገነባው የአኩሪ አተር ፕሮቲን እና የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ሥራውን ጀመረ። የፋብሪካውን ሥራ መጀመር “ትዊት” ያደረጉት የኢትዮጵያ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል፣ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር ምርቱን ኤክስፖርት በማድረግ 61 ሚሊየን 680 ሺህ ዶላር ለአገር እንደሚያስገኝ …

ተጨማሪ

የሲሚንቶ ፋብሪካ ኢንቨስትመንትን የሚከለክለው ሕግ ሊነሣ ነው

የሲሚንቶ እጥረትን ለማሻሻል እና እያደገ የመጣውን የሲሚንቶ ፍላጎት ለማሟላት በማሰብ፣ መንግሥት የአዳዲስ የሲሚንቶ ፋብሪካ ኢንቨስትመንቶችን የሚከለክለውን ሕግ ሊያነሣ መሆኑ ተገለጸ። ይህንኑ የሚያስረግጥ ማሻሻያ ደንብ ረቂቅ ለኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ቀረቦ ውይይት እንደተደረገበት ተነግሮኛል ሲል አዲስ ማለዳ ዘግቧል። በኬሚካል እና ኮንስትራክሽን ግብዓት የኢንዱስትሪ ልማት ተቋም የሲሚንቶ ኢንዱስትሪ ጥናት እና …

ተጨማሪ

ከአውሮፕላን ነዳጅ ውጪ የሌሎች የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ባለበት ይቀጥላል

Fuel

የነሃሴ ወር የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት እንዲቀጥል የተወሰነ ሲሆን የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ በነሃሴ ወር በሊትር በብር 26.50 (ሃያ ስድስት ብር ከሃምሳ ሳንቲም) እንዲሸጥ ተወስኗል፡፡ በዓለም ገበያ ላይ የሚኖረውን የነዳጅ ዋጋ መነሻ በማድረግ እንደአስፈላጊነቱ ማስተካከያ ሊያደርግ የሚችል መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የዜና ምንጭ፦ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የፌስቡክ ገጽ

ተጨማሪ

በአዲስ አበባ 125 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ እንደሆነ ምክትል ከንቲባው ተናገሩ

በአዲስ አበባ ከተማ በተመጣጣኝ ዋጋ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለማቅረብ 125 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በግንባታ ላይ እንደሚገኙ ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጅነር) ገለፁ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ሲሆን በዚህ ወቅት ምክትል ከንቲባው የ2012 በጀት አፈፃፀም ሪፖርት አቅርበዋል። በዚህ ሂደት ላይ …

ተጨማሪ

መንገዶች ባለሥልጣን በ10 ዓመታት የኢትዮጵያን ወረዳዎች ሁሉ በአስፋልት መንገዶች ለማገናኘት አቅጃለሁ አለ

በመጪዎቹ 10 ዓመታት ሁሉንም የኢትዮጵያ ወረዳዎች በአስፋልት መንገዶች ለማገናኘት እቅድ መያዙን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ። ከዚህም በተጨማሪ ከጎረቤት አገራት ጋር የሚያገናኙ መንገዶች ግንባታ ለማከናወንም መሪ እቅዱ ትኩረት እንደሚያደርግ ተገልጿል። ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በ10 ዓመቱ መሪ የልማት እቅድ ላይ እየተወያየ በሚገኘበት መድረክ ላይ እቅዱን አቅርቧል። ለሦስት ቀናት …

ተጨማሪ

ተቋርጦ የከረመው የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት ተመለሰ

በኢትዮጵያ ላለፉት ሦስት ሳምንታት ዝግ ሆኖ የቆየው የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት ተመለሰ። የድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን መገደል ተከትሎ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ውስጥ በተከሰተው አለመረጋጋት ሳቢያ የኢትዮጵያ መንግሥት የመደበኛና የሞባይል ኢንትርኔት አገልግሎቶችን በመላዋ አገሪቱ እንዲቋረጥ አድርጎ መቆየቱ ይታወሳል። ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ የዋይ-ፋይ የኢንተርኔት አገልግሎት መመለሱ ይታወቃል። በርካታ ተጠቃሚ ያለው የሞባይል ኢንተርኔት …

ተጨማሪ

የክልል ታርጋ ያላቸው ባለሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ተወሰነ

motorcycle

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የክልል ታርጋ ያላቸው ባለሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ወሰነ። የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ስጦታው አካለ በሰጡት መግለጫ የአዲስ አበባ ታርጋ ካላቸው የሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ውጭ ሌሎች ወደ መዲናይቱ መግባትም ሆነ በከተማዋ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም በተሰሩ ስራዎች እና በተከናወኑ ግኝቶች የክልል …

ተጨማሪ

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በ19.9 ቢሊየን ብር 12 መንገዶች ሊያሠራ ነው

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በ19.9 ቢሊየን ብር ወጪ 12 መንገዶችን ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት ፊርማ ከተቋራጮች ጋር ተፈራርሟል። የስምምነት ፊርማ የተከናወነባቸው 12ቱ የመንገድ ፕሮጀክቶች በድምሩ 825.23 ኪ.ሜ ርዝመት ያላቸው መሆኑም ታውቋል። ለግንባታው ከሚያስፈልገው ወጪ መካከል የአሥሩ መንገዶች በኢትዮጵያ መንግሥት የተሸፈነ ሲሆን፣ ሁለቱ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር ነው ተብሏል። የውል ስምምነቱን ከፈረሙት …

ተጨማሪ

ሸገር ዳቦ በ400 ማከፋፈያዎች እየተሰራጨ ነው ተባለ

የሸገር ዳቦ በተመጣጣኝ ዋጋ በ400 ማከፋፈያዎች ለአዲስ አበባና አካባቢው ነዋሪዎች እየተሰራጨ እንደሚገኝ ተገለፀ። የፋብሪካው ስራ አስኪያጅ ሲሳይ ደበበ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት፣ ሸገር ዳቦ ፋብሪካ የሚያመርታቸውን ዳቦዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች ማሰራጨት ጀምሯል። ፋብሪካው በዋነኛነት የዳቦ ዋጋን የኅብረተሰቡን ገቢ ባገናዘበ አነስተኛ ዋጋ የማቅረብ ዓላማን ይዞ እንደመግባቱ ተደራሽነቱ ላይ በጥብቅ እየተሠራ መሆኑን …

ተጨማሪ