ቅድስት ሰለሞን ልብስ ስፌት የተመሰረተው 2005 ዓ.ም በወ/ት ቅድስት ሰለሞን ነው። ድርጅቱ ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ በመልካም የእድገት ሁኔታ ምርት በማምረት ሂደት ላይ እንደሚገኝ የድርጅቱ መሥራች አባል ወ/ት ቅድስት ሰለሞን አስረድታለች። የመስራቿ የልብስ ስፌት እውቀት እንዲሁም የሥራ ልምድ ተደምሮ ድርጅቱ ሲመሰረት ከነበረው አንድ ማሽን አሁን ላለው አምስት ማሽን እና አራት …
ተጨማሪልምድ እና ተሞክሮ
የድር እና ማግ ሥራ – ሪል ድር ማጠንጠኛ
ሪል ድር ማጠንጠኛ የተመሰረተው 2005 ዓ.ም ሲሆን መስራቾቹም ሦስት አባላት ናቸው። ድርጅቱ ሁለት ዓመታት ያህል በጥሩ ሁኔታ ሲያመርት መቆየቱን የድርጅቱ መስራች አባል የሆነው አቶ ሀብታሙ አስረድቷል። የአቶ ሀብታሙ በሙያው ተገቢ የሥራ ልምድ መኖር፣ እንዲሁም የእህቱ የቴክስታይል ተማሪ መሆን እና በኳሊቲ ኮንትሮል በፋብሪካ ውስጥ ለረጅም ግዜ መሥራት ከባለቤቱ የሒሳብ ሥራ ክህሎት …
ተጨማሪ“ደንበኞችን ማርካት ዋና የቢዝነስ የማእዘን ራስ ነው”
ሳሙኤል ደባልቄ የሌዘር ሥራ ሳሚ የሌዘር ሥራ የተመሰረተው በ 2007 ዓ.ም ሲሆን፣ ድርጅቱ የምርት ሥራ የጀመረው በ2008 ዓ.ም ነው። የድርጅቱ መስራች የሆነው አቶ ሳሙኤል ሲያስረዳ በሙያው የትምህርት እንዲሁም የሥራ ልምድ በመቅሰም ወደ ድርጅቱ ምስረታ እንደመጣ ሳሚ ይናገራል። ሳሚ ሌዘር ሲመሰረት በአንድ ማሽን በራሱ መኖሪያ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት ሁለት …
ተጨማሪ“በደንብ የሚያውቁትን ስራ መሥራት ለውጤታማነት ቁልፍ ነው”
ሳሙዔል ሰማኸኝ (ሳሚ ማተሚያ ድርጅት) ሳሚ ሕትመት እና ተያያዥ ሥራዎች የተመሰረተው በ 2011 ዓ.ም ሲሆን፣ የተመሠረተውም የግል ኢንተርፕራይዝ ሆኖ በአቶ ሳሙኤል ሰማኸኝ ነበር። ድርጅቱ ሲመሰረት ሥራው ብዙም አስቸጋሪ እንዳልነበረ አቶ ሳሙዔል ይናገራል። የድርጅቱ መስራች የሆነው አቶ ሳሙዔል ወደ ሕትመት ሥራ ከመግባቱ በፊት በአይቲ (IT) ሥራ አራት ዓመት ሲሠራ እንደቆየ ያስረዳል። …
ተጨማሪየሚወዱትን የመሥራት እና የፅናት ውጤት
አሰገደች የልብስ ስፌት ሥራ ድርጅት አሰገደች የልብስ ስፌት የተመሰረተው በ 2005 ዓ.ም ሲሆን ድርጅቱ ሲመሰረት በሦስት መስራች አባላት እና በሦስት የልብስ ሲፌት ማሽኖች ነበር። ድርጅቱ በተመሰረተበት ወቅት ብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች እንደ ነበሩ ወ/ሮ አሰገደች ይናገራሉ። እንዲያም ሆኖ፣ እነዚህን አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቋቋሙ የዘለቀው ድርጅት በተሻለ ደረጃ ምርት ማምረት የጀመረው በ2009 ዓ.ም …
ተጨማሪ“ዓላማ፣ ትዕግሥት እና ጠንክሮ መሥራት እዚህ አድርሰውናል”
ኃይለገብርዔል፣ ፈረደ እና ጓደኞቻቸው እንጨት እና ብረታ ብረት ኃይለገብርዔል፣ ፈረደ እና ጓደኞቻቸው እንጨት እና ብረታ ብረት ኅብረት ሽርክና ማኅበር የተመሠረተው 1999 ዓ.ም መጨረሻ ላይ ነው – በ3,000 ብር ካፒታል። መሥራቾቹ፣ ድርጅቱ ሲመሠረት ብዙ ፈታኝ ሁኔታዎች እንደነበሩ ይናገራሉ። በተለይ የመደራጀት ችግር፣ መነሻ ካፒታል ማጣት፣ ብድር አለማግኘት ፣ የመሥሪያ ቦታ አለመኖር ወዘተ። …
ተጨማሪ