ወቅታዊ መረጃ

በዚህ ሥር፣ ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ ልዩ ልዩ ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ።

ኤጀንሲው የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል እንዲሁም የብድር ውሎችን ሰነድ አረጋግጦ የመመዝገብ አገልግሎት ላይ የአሠራር ለውጦች አደረገ

document-authentication

የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ከባንክ ውጪ የሚንቀሳቀስ ጥሬ ገንዘብን ሥርዓት ለማስያዝ ሲባል መንግስት የተለያዩ የማሻሻያ እርምጃዎች መውሰዱን ተከትሎ አንዳንድ የአሠራር ለውጦች አደረገ። ይህንኑ ተከትሎ ህገወጥነትን ለመከላከል እና ዘመናዊ አሰራርን ለማስፈን ሲባል ከዛሬ መስከረም 07 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ኤጀንሲው ባደረገው የአሰራር ማሻሻያ መሰረት የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል …

ተጨማሪ

በኮሮና ቫይረስ ለተጎዱ ኢንተርፕራይዞች የቀረበ ዝቅተኛ ወለድ እና እፎይታ ያለው ብድር

በኮሮና ቫይረስ ወረሽኝ የተነሣ በደረሰው የንግድ መቀዛቀዝ ውስጥ፣ ሥራቸውን ለመቀጠል እየጣሩ ያሉ ጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ለመደገፍ የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን፣ ማስተርካርድ ፋውንዴሽን እና ፈርስት ኮንሰልት በጋራ ኢንተርፕራይዞቹ ድጋፍ የሚያገኙበት ፕሮጀክት አዘጋጅተዋል። በፕሮጀክቱም መስፈርቱን የሚያሟሉ ኢንተርፕራይዞች ዝቅተኛ ወለድ እና የእፎይታ ጊዜ ያለው ብድር ተመቻችቶላቸዋል። በዚህም መሠረት፡- የሠራተኞች ብዛት፡- ከ 2 …

ተጨማሪ

ከወጪ ንግድ ወደ 4 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት ታቀደ

export-containers

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተያዘው የ2013 በጀት አመት ከ ወጪ ንግድ 3.91 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት በዕቅድ መያዙን አስታወቀ። ከዚህም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ድጋፍና ክትትል ከሚያደርግባቸው የግብርና 2.918 ቢሊዮን እና የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ምርቶች 587.5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚጠበቅ ጨምሮ አስታውቋል ፡፡

ተጨማሪ

ፓልም የምግብ ዘይት ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ በሃገር ውስጥ በከፊል ሊመረት ነው

መንግስት በዜጎች ላይ የኑሮ ውድነት እንዳይፈጠር መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦችን በድጎማ ከውጪ ከሚያሥገባቸው ሸቀጦች ውስጥ አንዱ የሆነውን ፓልም የምግብ ዘይት ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ በሃገር ውስጥ ለማምረት እንቅስቃሴ መጀመሩን በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ትራንስፎርሜሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬከተር አቶ አድማሱ ይፍሩ ተናገሩ፡፡

ተጨማሪ

በመስከረም ወር ከአውሮፕላን ነዳጅ ውጪ የሌሎች የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ባለበት ይቀጥላል

Fuel_Tanker

የመስከረም ወር የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት እንዲቀጥል የተወሰነ ሲሆን የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ በመስከረም ወር በሊትር በብር 26.97 (ሃያ ስድስት ብር ከዘጠና ሰባት ሳንቲም) እንዲሸጥ ተወስኗል፡፡ በዓለም ገበያ ላይ የሚኖረውን የነዳጅ ዋጋ መነሻ በማድረግ እንደአስፈላጊነቱ ማስተካከያ ሊያደርግ የሚችል መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የዜና ምንጭ፦ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚንስቴር የፌስቡክ ገጽ

ተጨማሪ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በቡና መቀበያ ቅርንጫፎች የቡና ናሙና ማሳያ ሥራ ላይ አዋለ

green-coffee-bean

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በቡና መቀበያ መጋዘኖች ለውጪ ገበያ የሚቀርብ የቡና ምርት ናሙና ማሳያ (Sample Display) አዘጋጅቶ ከነሐሴ 13 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለደንበኞች አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ በግብይት ሥርዓቱ ላይ የደንበኞችን ፍላጎት በማሟላት የወጪ ንግዳችንን ለማሳደግ የሚከናወኑ የማሻሻያ ሥራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል በአቅራቢዎች፣ በገዢዎችና በምርት ገበያው መካከል ያለውን የአሰራር ግልጽነት ለማጠናከር ይህ …

ተጨማሪ

የሲሚንቶን እጥረት ለመቅረፍ እየተሠራ ነው – ንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር

cement-bag

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በኢትዮጵያ የተፈጠረውን የሲሚንቶ ችግር ለመቅረፍ የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑን ገለጹ፡፡ ለሲሚንቶ እጥረት መከሰት በዋናነት የመለዋወጫ ችግር፣ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ፣ የግብዓት እጥረት ፣ የአመራርና የባለሙያ የክህሎት ክፍተት መኖር፣ የፀጥታ ችግር፣ የጥሬ እቃ አቅርቦት እና ሌሎች ችግሮች መኖራቸው ነው ያሉት አቶ መላኩ ችግሩን ለመቅረፍ …

ተጨማሪ

ኔዘርላንድስ ከኢትዮጵያ በመግዛት ቀዳሚ ሀገር ሆነች

የ2012 በጀት ዓመት የወጪ ንግድ ከፍተኛ ገቢ በማስገኘት ኔዘርላንድስ ቀዳሚ ሀገር ሆናለች ተባለ፡፡ አበባ፣ ቡና፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ የኤሌክትሪክ ውጤቶች፣ ጫማ፣ ቆዳ፣ ማርና ሰም፣ የቅባት እህሎች፣ የአልኮል መጠጦች፣ ጫት፣ ሻይ፣ ብረትና የመሳሰሉትን ከኢትዮጵያ በመቀበል 320,162.35 የአሜሪካን ዶላር በማስግኘት ቀዳሚ ሀገር ሆናለች፡፡ ጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ ቡና ጫማ፣ አበባ፣ የቆዳ ውጤቶችን፣ የቅባት …

ተጨማሪ

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ የቆዳ ፋብሪካዎችን ጎበኙ

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እና የአግሮ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ ሚ/ዴኤታ አቶ ተካ ገ/የስ ትናንትና ነሐሴ 15 ቀን 2012 ዓ.ም በተለያዩ የቆዳ ፋብሪካዎች ተገኝተው የስራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ ለግማሽ ቀን በቆየው የስራ ጉብኝት ላይ የውጭ ምንዛሬ፣ የመሬት፣ የመብራት መቆራረጥ፣ የተማረ የሰው ኃይል፣የመስሪያ ካፒታል ችግሮች እንዳሉ በዘርፉ ተዋንያኖች የተጠቆመ ሲሆን እነዚህንና መሰል …

ተጨማሪ

ከአውሮፕላን ነዳጅ ውጪ የሌሎች የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ባለበት ይቀጥላል

Fuel

የነሃሴ ወር የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት እንዲቀጥል የተወሰነ ሲሆን የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ በነሃሴ ወር በሊትር በብር 26.50 (ሃያ ስድስት ብር ከሃምሳ ሳንቲም) እንዲሸጥ ተወስኗል፡፡ በዓለም ገበያ ላይ የሚኖረውን የነዳጅ ዋጋ መነሻ በማድረግ እንደአስፈላጊነቱ ማስተካከያ ሊያደርግ የሚችል መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የዜና ምንጭ፦ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የፌስቡክ ገጽ

ተጨማሪ